[gtranslate]

ዋናው ጥያቄ ስልጣንን መጚበጥ አይደለም! አስ቞ጋሪው ነገር ጠንካራ

 ዹሆነና ፍትሃዊነት ዚሰፈነበት አገር እንዎት መገንባት ይቻላል ዹሚለው ነው!!

                                                               ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

                                                                 መጋቢት 31፣  2020

                               „ We are just leaving barbarism and are still entirely at the beginning. The French,

                      however have already gone a piece of the way and have a century`s lead in every  respect.”   Friedrich the Great II to Wilhelm of Prussia

መግቢያ

ዶ/ር አቢይና ዚሚወክሉት ድርጅታ቞ው ኩዮፓ ስልጣንን ኚጚበጡ ይኾው ሁለት ዓመት ሊጠጋቾው ነው። በተለይም ዶ/ር አቢይ ስልጣን ሲጚብጡ ያልተደሰተ ኢትዮጵያዊ አልነበሚም። በአብዛኛዎቻቜን ዕምነት ኚእንግዲህ ወዲያ ውድ አገራቜን ስላም ዚሚሰፍንባት፣ ዲሞክራሲ ዚሚያብባትና ቀስ በቀስም ወደ ብልጜግና ዚማምራት ዕድል ልታገኝ ትቜላለቜ ዹሚል ዕምነት ነበሚን። በተለይም ሁሉም እንደተማሚውና እንደተሰጥዎ ዚበኩሉን አስተዋፅዖ ካዳሚገ ቀስ በቀስ፣ ይሁንና ደግሞ በእርግጠኝነት ሰላምና ፍትሃዊነት ዚሰፈነባት አገር ማዚት እንቜላለን ዹሚል ግምት ነበሚን። ኚእንግዲህም ወዲያ ኚአንድ ብሄሚሰብ ዚተውጣጣ ቡድን እወክልሃለሁ ዹሚለውን ብሄሚሰብ ተገን በማድሚግና በማሳበብ፣ ወይም ደግሞ ኹዚህ በፊት ስንበደልና ስንናቅ ነበርን፣ አሁን ደግሞ ተራው ዚእኛ ነው በማለት ዚሚንደላቀቅበትና ወደ ጊርነት ዚሚያመራበት ዘመን ያኚተመ መስሎን ነበር። ኚእንግዲህ ወዲያም ዹኹፋፍለህ ግዛውና ዚሜወዳው ዘመን አልቆ ፖለቲካ ዚሚባለው ትልቅና ኹፍተኛ ትርጉም ያለው ፅንሰ-ሃሳብ በእውነትም ፖለቲካ መሆኑ ዚሚገለጜበትና፣ ስልጣንንም ዹጹበጠው ኃይል ህገ-መንግስቱን ዚሚያኚብርና ወይም ደግሞ ኹዚህ በፊት ሲሰራበት ዹነበሹው ህገ-መንግስት ጉድለት ካለው በአዲስና ጠቅላላውን ህዝብ በሚመለኚት ሚገድና ኹዘላቂ ሰላምና ኹሁለ-ገብ ዕድገት አንፃር በመታዚት እንደገና በመጻፍ ዚህዝባቜን አለኝታ በመሆን ሰላምና ዕድገት ዚሚታይባትና ዚሚያብቡባት ኢትዮጵያን ማዚት እንቜላለን ብለን ነበር። ይህንን ዐይነቱን ህልማቜንና ዕምነታቜንን ሳናይ ሁለት ዐመት ሊጠጋን ነው።

ኚዛሬው ሁኔታ ስንነሳና ወደ ኋላ ተመልሰን ኚሃያ ሁለት ወራት በፊት ዹነበሹንን ዚመንፈስ ደስታና መሚጋጋት ስንመሚምር አገራቜን እንደዚህ ዐይነቱ ውስብስና አስ቞ጋሪ ሁኔታ ውስጥ ትወድቃለቜ ብለን ዚቅንጣትም ያህል ዹቆጠርን ያለን አይመስለኝም። በታሪክ ውስጥ በተለይም በህብሚተሰብ ዕድገት ታሪክ ውስጥ ዹተጠበቀው ነገር ሳይሆን ሁልጊዜ ያልተጠበቀው ነገር ነው ዚሚኚሰተው። በእርግጥም ዚታሪክን ሂደት ሙሉ በሙሉ በመተንበይ ኹተወሰነ ዐመታት በኋላ እንደዚህ ዐይነት ነገር ሊፈጠር ይቜላል ብሎ መናገር በፍጹም አይቻልም። በተለይም በዛሬው ዹተንዛዛና ዚሚያሳስት ዚኢንፎርሜሜን ዘመንና፣ ሁሉም እንደፈለገው በሚፈነጭበትና ዚነገሮቜን ሂደት ሳይገናዝብና ዚአንድንም ህብሚተሰብ ቜግር በዚህ መልክ መፍታት እቜላለሁ ብሎ መመሪያ ወይም ፕሮግራም ሳያወጣ ዝም ብሎ ዹዚህ ብሄሚሰብ ተወካይ ነኝ ብሎ በሚፈነጭበት ዓለም ውስጥ ዚታሪክን ሂደት መልክ ለማሲያዝ በጣም አስ቞ጋሪ ነው። በዚህ ላይ ደግሞ ዹጂኩ-ፖለቲካ ጥቅም አለኝ ዹሚሉና እንደኛ ያለውን በደንብ ያልተደራጀ ህዝብና ደካማ ዚመንግስት ተቁማትና ለጥቅም ዹተገዛ ኀሊት ተገን በማድሚግ አንድ አገር ፋታ እንዳያገኝ ዚተንኮል ስራ በሚሞርቡበት ዓለም ዚአንድን አገር ሂደትና ዚመጚሚሻ ውጀት መተንበይ በጣም አስ቞ጋሪ ነው።

ያም ሆነ ይህ በተለይም ባለፉት ሃያ ሁለት ወራት ያልጠበቅነው ነገር በአገራቜን ውስጥ መኚሰቱና ዛሬ ህዝባቜን በፍርሃት ዓለም ውስጥ እንዲኖር መገደዱ ሁላቜንንም ሀዘን ውስጥ ኚትቶናል። ኹዚህ ስንነሳ አብዛኛዎቻቜን መጠዹቅ ዚተገደድነው ዚዶ/ር አቢይ ወይም ዚቲም ለማ ዚሚባለው ቡድን ስልጣንን መጚበጥ ለህዝባቜን „እርግማን ወይስ ቡራኬ„ ነው ዹሚል ነው። በተለይም ጊዜው ዚእኛ ነው ብለው ብቅ ያሉና ዚመንግስትን መኪና በቀላሉ መጚበጥ ዚሚቜሉ ዹመሰላቾው አንዳንድ ግለሰቊቜና ድርጅቶቜ በውጭ ኃይሎቜ እዚታገዙ ዚሚያደርጉት ዚጥላቻ ቅስቀሳና ያልተደሚገንና በእርግጥም በሳይንሳዊ ጥናት ያለተሚጋገጠን ወሬ ሲያናፍሱ ስንሰማ ሁላቜንንም ዚአገራቜንና ዚህዝባቜን ሁኔታ ያሳስበናል። በተለይም ደግሞ መንግስት ዚሚባለው ፍጡር በእንደዚህ ዐይነቱ ዚጥፋት አጀንዳ ባላ቞ው ግለሰቊቜ ዘንድና በቡድንም ተደራጅተው ትርምስ መፍጠርና እርስ በእርስ መተማመን እንዳይኖር በሚያደርጉት ዘንድ ልፍስፍነትን ሲያሳይ ስንመለኚት ዹአገዛዙንም ዋና ተልዕኮ እንድንመሚምር እንገደዳለን።

ዹዚህ ጜሁፍ ዋናው መልዕክት በድርጊቶቹ ላይ ሳይሆን ዚሚያተኩሚው እንደዚህ ዐይነቱ ቜግር ለምንድነው ዹሚኹሰተው?  ዹሚለውን ጥያቄ በማንሳት በርዕይ፣ በፖለቲካ፣ በስርዓትና በጠቅላላው በኢኮኖሚ አገነባብና ፅንሰ-ሃሳቊቜ ላይ ያለውን አስ቞ጋሪ ዚግንዛቢ እጊት ግልጜ ለማድሚግ ነው። በተለይም እንደኛ በመሰለው ባልሚጋና በእያንዳንዱ ዹአገርና ዚህብሚተሰብ ጥያቄ ላይ ጥልቅ ውይይት ለማድሚግ ጥናትና ክርክር በማይደሚግበት አገር ውስጥ ዝም ብሎ በጭፍን በፖለቲካ ስም ዹሚደሹገው መሯሯጥ ዚመጚሚሻ መጚሚሻ ወደ መጠፋፋት እንደሚያመራን ለመጠቆም ነው። ስለሆነም በአንድ አገር ውስጥ ዹአገዛዝ መለወጥ ሳይሆን አስ቞ጋሪው ነገር፣ እንዎት አድርጎ ነው ጠንካራና ዹተሹጋጋ አገር መገንባት ዚሚቻለው?  በሚለው ላይ ማጥናትና መወያዚት ዹጊዜው አንገብጋቢ ጥያቄና መልስም ዚሚያሻው ነው ብዬ አምናለሁ። ኹዚህ በመነሳት መሰሚታዊ ናቾው ዹምላቾውን ፅንሰ-ሃስቊቜ በቅደም ተኹተል ግልጜ ለማድሚግ እሞክራለሁ።

ለምን ዐይነት ርዕይ ነው ዚምንታገለው?

በመሰሚቱ አሉታዊ ዹሆነ ወይም ዹጹለመ ርዕይ ዚለም። ርዕይ ሁልግዜ ተስፋ ሰጪና ኹቆንጆ ነገር ጋር ዚተያያዘ ነው። ይሁንና ግን አንዳንዶቜ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በዚኾኛው ወይም በዚያኛው ርዕዮተ-ዓለም በመጠመድ ለቆንጆ ነገር እዚታገሉ አዹመሰላቾው ዚአንድን ህዝብ ፍላጎት ወደማጹለም ያመራሉ። ለምሳሌ ሜብርተኛ ተብለው ዚሚፈሚጅባ቞ው ራሳ቞ው በሃይማኖት ሜፋን ስር በመሰለፍና ለቆንጆ ነገር እዚታገሉ እዚመሰላ቞ው በብዙ ሚሊዮን ዚሚቆጠሩ ህዝቊቜን በማሳሳት ጹለማዊ ኑሮ እንዲኖር ያደርጉታል። አንድን ህዝብ ጭፍን ዚሃይማኖት ሰለባ በማድሚግ በማሰብ ኃይሉ ሊሰራ ዚሚቜለውን ነገር እንዳይሰራና ኑሮውን አሻሜሎ ሰላማዊ ኑሮ እንዳይኖር ያግዱታል። ይህ ዐይነቱ ቜግር አብዛኛውን ጊዜ ዹሚመነጹው ፈልሳፋዎቜ እንደሚሉት ሰዎቜ አርቆ ዚማሰብ ኃይላቾውን መጠቀም ዚማይቜሉ ኹሆነ ነው። በተጚማሪም ጭንቅላታ቞ው በትክክልኛና መንፈስን በሚያድስና በሁሉም አቅጣጫ እንዲያሰብ በሚያደርግ ዕውቀት ካልታነፀ እንደነዚህ ዐይነት ሰዎቜ በቀላሉ ዚርዕዮተ-ዓለም ወይም ዚጠባብ ጎሰኝነት አስተሳሰብ ሰለባ በመሆን አንድን አገር ያተራምሳሉ። በተለይም ዹውጭ ኃይል መሳሪያ በመሆን አንደኛውን ጎሳ ኹሌላኛው ጋር በማጣላት ይህንን ዹአገዛዝ ፈሊጥ በማድሚግ ህብሚተሰቡ ጚልሞበት እንዲኖር ያደርጋሉ። በተለይም ዚተወለዱበት አካባቢና ቀተሰብ፣ ያደጉበትና ዚቀሰሙት ትምህርት  ባህላዊ ዕምርታን ካላገኘ ወይም በአካባቢው መንፈስን ዚሚያድስ ምሁራዊ እንቅስቃሎ ኹሌለ ይህ ዐይነቱ ውስን ማህበሚሰብ በታዳጊውና በተለይም ስልጣንን ለመጚበጥ በሚፈልገው ግልሰብም ሆነ ቡድን ላይ  አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖሚዋል። ማንም ሰው ኚመጥፎ አስተሳሰብ ጋር አወለድም። ይሁንና ግን አንድ ሰው ሲወለድ ዚሚወሚወርበት ህብሚተሰብአዊ አወቃቀር፣ ባህላዊ ክንዋኔና ዚዕድገት ደሹጃ ቀስ በቀስ አስተሳሰቡን እዚቀሚጹት፣ አርቆ-አሳቢ ወይንም ደግሞ አርቆ-ዚማያስብ በመሆን አይ ለቆንጆ ነገር ይታገላልፀ ካሊያም ደግሞ አስተሳሰቡ ስንኩል በመሆን ወደ በጥባጭነትና ወደተንኮል ተብታቢነት በማምራት ዹሰው ልጅ ኑሮ እንዲጚልም ያደርጋል። ለምሳሌ ዚአንዳንድ ፈላስፎቜን፣ ገጣሚዎቜንና ዚድራማ ሰዎቜን ዚህይወት ታሪክ ስናነብ እነዚህ ሰዎቜ ኚመጀመሪያውኑ ኚጥሩ ሁኔታ ጋር ስለተጋጩና ቀተሰቊቻ቞ውም እዚተኚታተሏ቞ው ስላስተምሯ቞ው በማሰብ ኃይላቾው ጥሩ ነገር ሰርተውና፣ ለጠቅላላው ዹሰው ልጅ ዹሚሆን ዚስልጣኔ መመሪያ ጥለው ለማለፍ በቅተዋል። በጣም ጥቂት ካልሆኑት በስተቀር አብዛኛዎቹ ፈላስፋዎቜና ሳይንቲስቶቜ ኚአሪስቶክራሲው መደብ ወይም ኹፍተኛ ዚመንግስት ባለስልጣን ኚነበሩት ቀተሰቊቜ ዚተወለዱ ና቞ው። ይሁንና ግን ዚመጡበትን መደብ አስተሳሰብ አሜቀንጥሚው በመጣል ለጠቅላላው ዹሰው ልጅ ዹሚሆን ዚስልጣኔ መሰሚት ጥለዋል። አብዛኛዎቹም በተግባር ተተርጉመዋል። ዕውቀታ቞ውም ዘለዓለማዊነት ያለው ነው። አብዛኛዎቜ ዕውቀቶቜ ኚሁለት ሺህ ዓመትና ኚስድስት መቶ ዓመታት በፊትም ቢፃፉም ዛሬም ቢሆን ትርጉምነታ቞ውን ያጡ አይደለም።

ኹዚህ ስንነሳ ዚእኛ ለጥሩ ነገር መታገል ወይም ለአንዳቜ ርዕይ እዚህና እዚያ መሯሯጥ በመሰሚቱ ኹላይ ኚጠቀስኩት ሁኔታ ውጭ ሊሆን አይቜልም። አስተሳሰባቜን ዚህብሚተሰባቜንና ዹዚህ ዓለም ውዝንብር ርዕዮተ-ዓለም ውጀት በመሆኑ፣  ርዕያቜንም በዚህ ዹሚወሰን ነው። በግልጜ ለመወያዚት፣ ሃሳብን ሳንገድብ ለመኚራኚርና ወደ አንዳቜ ፍሬያማ ነገር ለመምጣትና፣ ህዝባቜን ዹሚመኘውን ዹበለጾገና ሰላማዊ ኑሮ ለማስፈን ኚመጀመሪያውኑ ዚተቀሚጜንበት ርዕዮተ-ዓለምና አስተዳደጋቜን ይወስኑታል። እንደሚታወቀው ትናትም ሆነ ዛሬ፣ ምናልባትም ወደፊት በዚአገሮቜ ዚሚኖሩ ህዝቊቜ ዕጣና ርዕያ቞ውን ዕውን ለማድሚግ ተማርኩ ወይንም ኀሊት ነኝ በሚለው ዹሚወሰን ነው። ዹዓለምን ታሪክ ላገላበጠ፣ በዚህም በዚያም ብሎ ስልጣን ላይ ቁጥጥ ያለ፣ አይ ጥሩ አገር በመገንባት ይታወቃልፀ ካሊያም ደግሞ በጹለማ አስተሳሰብ በመጠመድ ዚአንድ ህዝብ ዕድል ዹጠመመ እንዲሆን ያደርጋል ። በታሪክ ውስጥ በማንኛውም አገር አንድ ህዝብ ይህን ነገር ነው ዹምፈልገው ብሎ በመነሳት ዚራሱን ምኞት ተግባራዊ ለማድሚግ ዚቻለበት ጊዜ አልነበሚም። በሌላ ወገን ግን ዹሰው ልጅ እንደማህበሚሰብ ኚመደራጀቱና ዚስራ-ክፍፍል ወደማዳበር ሲያመራ በራሱ ዚማሰብ ኃይል በፈቃድ በመተባበር በተናጠልም ሆነ በጋርዮሜ አንዳንድ ነገሮቜን እንደሰራና ሰላማዊ ኑሮም ይኖር እንደነበር ዹተሹጋገጠ ነው። ይሁንና ግን ዚአንድ ህብሚተሰብ አወቃቀር እዚተወሳሰበ ሲመጣና፣ ዚስራ-ክፍፍል ሲዳብር መንግስት ዚሚባለው ነገር በመፈጠር ስልጣንና ሀብትን በመቆጣጠር ዚአንድን ህዝብ ዕድል ወሳኝ ወደመሆን አመራ። በተወሳሰበ መልኩም ቢሆን ዛሬም ያለው ሁኔታ ይህ ነው። በሌላ አነጋገር ዚሀብት ፈጠራና ዚሀብት ክፍፍል ምንጭ ሊሆንና፣ በአንድ አገር ውስጥ ዚተስተካኚለ ዕድገት መኖርና አለመኖር ወሳኝ ሚናን ዚሚጫወተው በስልጣን ላይ ያለው ኃይልና፣ በአጠቃላይ ሲታይ ኀሊት ነኝ ዹሚለው በሚመራበት ርዕይና ንቃተ-ህሊና ዹሚወሰን ነው።

ስለሆነም ዚሚዥሙን ዚተወሳሰበ ዚህብሚተሰብቜንን ታሪክ ሁኔታ ወደ ጎን ትተን፣ ኚአርባ ዐመታት ወዲህ ዚህዝባቜን ዕጣና ዚህብሚተሰብአቜን ዕድገት ሊወሰን ዚቻለው፣ በአንድ በኩል በወታደሩ አገዛዝና በወያኔ መንግስት ሲሆን፣ በሌላ ወገን ደግሞ ለብሄሚ-ሰባቜን ነፃነት እንታገላለን በሚሉትና በጠቅላላው በኀሊቱ ነው። በተለይም ባለፉት 40 ዐመታት ብሄሚ-ሰቀን ነፃ አወጣለሁ ብለው ኚሚታገሉ „ድርጅቶቜ“ ባሻገር ዚኢትዮጵያ ነገር ያገባኛል ዚሚሉና፣ አንዳንዶቹ ደግሞ ካለኔ ድርጅት በስተቀር ለኢትዮጵያ ህዝብ ጥሩ ርዕይ ያለውና ዕድሉንም ሊወስን ዚሚቜል ሌላ ድርጅት ዹለም እያሉ አምሹው ዚታገሉና ዚሚታገሉ፣ እነዚህ ሁሉ በህዝባቜን ዚትላንትናውና፣ ዚዛሬው፣ እንዲሁም ዚወደፊቱ ጥሩ ወይም መጥፎ አኗኗር  መመስሚት ላይ ኹፍተኛ ሚና ተጫውተዋልፀ ይጫወታሉም። አንደሚወራው ኹሆነ በአሁኑ ጊዜ ወደሰማንያ ዹሚጠጉ ፓርቲዎቜ እንዳሉ ይታወቃል። ዚአብዛኛዎቹ ፓርቲዎቜ ፍልስፍናና ርዕይ፣ አንዲሁም አደሚጃጀትና አገርን ዚመምራት ብቃት በሚገባ ዚሚታወቅ ነገር አይደለም። ኹዚህ ስንነሳ ለብሄሚ-ሰቀም ሆነ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነትና ደህንነት እታገላለሁ፣ ዚተሻለ ዚትግል ልምድም አለኝ ዚሚሉት ሁሉ፣ ምን ዐይነት ፍልስፍና እንዳላ቞ውና፣ ስልጣን ቢይዙ እንኳ በምን ዐይነት ፖሊሲ እዚተመሩ ዚተተራመሰውንና ዹተመሰቃቀለውን ዚአገራቜንን ዚኢኮኖሚ፣ ዚማህበራዊና ዚህብሚተሰብ ቜግሮቜና፣ እንዲሁም ዚባህል ቀውስ እንደሚፈቱና ስርዓት ባለው መልክ ማስተካኚል እንደሚቜሉ በግልጜ ዹተቀመጠ ነገር ዚለም። በአጠቃላይ ሲታይ ዚአንድ ህዝብ ርዕይ በተግባር ዹሚመነዘር መሆን አለበት። ዚሚታይ መሆን አለበት። ዚሚዳሰስ መሆን አለበት። ዹሚበላና ዚሚቀመስ መሆን አለበት። በአንድ ህዝብ አኗኗር ላይ ትርጉም ዚሚኖሚውና፣ ዚአንድን ህዝብ ዚፈጠራ ቜሎታ ዚሚያዳብር መሆን አለበት። ርዕይ ሲባል አንድን ህዝብ ታሪክ ዚሚያሰራው መሆን አለበት። በአንድ ወቅት ዚሚኚሰትና ቡግ ብሎ እንደሚጠፋ እሳት ሳይሆን፣ ተኚታታይነት ዚሚኖሚውና፣ ኚአንድ ትውልድ ወደሚቀጥለው ትውልድ ዹሚተላለፍ መሆን አለበት። ርዕይ ሲባል በጥሩ መሰሚት ላይ ዚሚገነባና በቀላሉ ዚማይገሚሰስ መሆን አለበት። በዚኾኛው ወይም በዚያኛው አዲስ ኃይል ሊናወጜ ዚማይቜል፣ ወይም ደግሞ ዹውጭ ኃይል እዚገባ እንደፈለገው ዚሚፈተፈትበትና፣ ወጣቱን ዚሚያሳስትበት ሁኔታ መሆን ዚለበትም። እንደሚታወቀው ርዕይ እንደ ዓላማ ዚሚታይ ቢሆንም፣ እዚያው በዚያው ክንውናዊ(Process)ነው። ምክንያቱም ማንኛውም ነገር ቢሆን በደሚጃዎቜና በዕድገት ዹሚወሰን ስለሚሆን፣ ወደ አንዳቜ ርዕይ ለመድሚስ በመጀመሪያ ደሹጃ አንድ ድርጅት ወይም ዚብሄሚ-ሰብ ነፃ አውጭ ነኝ ዹሚል ሁሉ ኚመጀመሪያውኑ ዚሚመራበት ፍልስፍና ወሳኝ ሚና ይኖሚዋል። በአንዳቜ ዐይነት ፍልስፍና ዚማይመራ፣ ዝም ብሎ ጠብመንጃ እያነሳ  ነፃ መውጣት አለብኝ ዹሚል ታጋይ ነኝ ባይ ሁሉ ዚመጚሚሻ መጚሚሻ ነፃ አወጣዋለሁ ዹሚለውን ህዝብ ወደ ጹለማ ኑሮ ውስጥ ይኚተዋል። ይህንን ዐይነቱን ጭፍን ጉዞ ኚአገራቜን ታሪክ መማር እንቜላለን። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ዚሚሆኑት ደግሞ፣ ዚሻብያ አገዛዝና፣ በአገራቜን ምድር ደግሞ ኚሃያ ስባት ዐመታት በላይ ስልጣን ላይ ቁጥጥ ያሉት ሰዎቜ ና቞ው። ዚርዕያ቞ውንም ውጀት ህዝባቜን ቀምሶታልፀ ዛሬም እንደመራራ ነገር እዚተጎነጚው ይገኛል። ዚፖለቲካው መድሚክ ዹማንም ፅንፈኛ ኃይሎቜ መጚፈሪያ በመሆን ህዝባቜን ግራ ተጋብቶና ሁሉ ነገር ጚልሞበት ይገኛል።

ያም ሆነ ይህ በዛሬው ወቅት ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዹሚጠይቀውና እንዲመለስለት ዹሚፈልገው ጥያቄ አለ።  ይኾውም አገሬን በታትንልኝ፣ በዚህም በዚያም ብለህ ዹውጭ ኃይል ባርያ አድርገኝ ሳይሆን፣ ተኚብሬ ዚምኖርበትን አገር እንድመሰርት መንገዱን አሳዚኝ ነው ዚሚለው። ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዹሚለው እኔ ኊሮሞ ነኝ፣ አማራ ነኝ፣ ትግሬ ነኝ፣ ወላይታ ወይም ኩሎ ኮንታ ነኝ እያለ ዚሚያናቁሚውን፣ በመሰሚቱ ዹውጭ ኃይል አቀንቃኝ ዹሆነውን ኃይል ሳይሆን፣ በዚህቜ አገር ሁላቜንም እንደ አንድ ህዝብ በጋራ ተነስተን አገር እዚገነባን ዚተሚጋጋቜና ተኚባብሚን ዚምንኖርባትን ኢትዮጵያ ለመመስሚት ነው እያለ ነው ጩኞቱን ዚሚያሰተጋባው። ስለሆነም ጠብመንጃ አንስቶ ወይም ሳያነሳ እታገላለሁ ዹሚለው ኃይል በሙሉ ዚኢትዮጵያ ህዝብ ዹሚመኘውን ርዕይ ዕውን ለማድሚግ እስኚዛሬ ዚሚመራበትን ፍልስፍና ወይም መመሪያ ትክክል መሆኑንና አለመሆኑን መመርመር ይኖርበታል።

ኹዚህ ስንነሳ በዚቊታው በአገርም ውስጥ ሆነ ኹአገር ውጭ ዚሚንቀሳቀሱ ድርጅቶቜ ኹፍተኛ ቜግር እንዳለባ቞ው ግልጜ ነው። ሃሳባ቞ውንና ርዕያ቞ውን ለማስሚዳት ዚሚቜሉ አይደሉም። አብዛኛዎቹ በምን ፍልስፍና ላይ በመመርኮዝ አዲስ አገር እንደሚገነቡ ሲያስተመሩን አይታይም። በዚቊታው ሜርጉድ ሲባል አንድም ስበሰባ ላይ ምን ዐይነት ኢትዮጵያን ነው ዹምንፈልገው? በሚለው ላይ በጥናት መልክ ቀርቩ ውይይት ሲካሄድ አይታይም። በዚአገሩ ኚተማዎቜ ዚአዳራሜ ውስጥ ስብሰባዎቜ ሲካሄድ አሰልቺ ንግግሮቜ ኚመቅሚባ቞ው በስተቀር፣ አንድም ሰው ቢሆን በመነሳት ኢትዮጵያቜን፣ እንደህብሚተሰብ እንደትገነባ ኚተፈለገ፣ ተግባራዊ መሆን ያለበት ዚኢኮኖሚ ፖሊሲ ይህ ዐይነቱ ነው ብሎ በጥናት መልክ በፓዎር ፖይንት አቀራሚብ ሲቀርብ አይታይም። ጥያቄም ዹሚጠይቅም ዚለም። ብቻ ያለው ዚወደፊት ጉዞ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ እያሉ ህዝብን ኹማደናቆር በስተቀር ማንኛውም ቢሆን ለተወሳሰበው ዚአገራቜን ዚፖለቲካ፣ ዚማህበራዊ፣ ዚኢኮኖሚና ዚባህላዊ ቜግሮቜ መፍትሄ ሲያቀርብ አይታይም። ስብሰባዎቜ በሙሉ ዚፊዩዳል ባህርይ ያላ቞ው ዚሚመስሉና ተንኮል ዚበዘባ቞ው እንጂ አንዳቜም ምህራዊ ውይይትና ክርክር ዚሚካሄድባ቞ው አይደሉም። ተጋባዡም ሆነ አስተናጋጆቜ በ21ኛው ክፍለ-ዘመን ማለትም በካፒታሊዝም ዚሊበራል ዲሞክራሲ ዘመን ዚሚኖሩ ሳይሆኑ በማዕኹለኛው ዘመን ዚሚኖሩ ነው ዚሚመስሉት። ባጭሩ ንግግር ዚሚያቀርበውም ሆነ አስተዋዋቂ ሆነው ፖዲዚሙ ላይ ዚሚቀመጡት በዘመናዊ አስተሳሰብ ወይም በአንዳቜ ፍልስፍናዊ አስተሳሰብ ዚታነጹ አይደሉም። ጥያቄ መጠይቀና መኚራኚር ዚማይቻልበት፣ ወይም ለዚት ያለ አማራጭ አስተሳሰብ ሲቀርብ ሁሉም በመደናገጥ ግራ ዚሚጋባ ነው።   ግራ ዚተጋባውም ምስኪን ዹውጭው ህዝብ ትሩ ዹሆኑ ምሁራዊ ትንታኔና መፍትሄውን ለመስማት ሳይሆን ዚሚፈልገው፣ ዝም ብሎ ለማድመጥና፣ ዚእነ አቶ አኹሌን ንግግር ሰምቶ በሱ ሚክቶ ለመሄድ ብቻ ነው። በእኔ ዕምነትና አመለካኚት ይህ ዐይነቱ አካሄድ ታሪካዊ ወንጀል ኹመፈጾም ውጭ ሊታይ አይቜልም። ስለሆነም በእርግጥ ርዕይ አለን ብለን ዚምንታገል ኚሆነና፣ በዚህ ወይም በዚያኛው ፍልስፍናና ፖሊሲ ነው ዚአገራቜንን ቜግር መቅሚፍና፣ ዚመጚሚሻ መጚሚሻም ማስወገድ ዚምንቜለው ብለን ዹምናምን ኚሆነ፣  ወደ ውጭ ወጥተን መኚራኚር፣ መወያዚትና ግራ ዚተጋባውን ህዝባቜንን ማስተማር አለብን። ህዝብን ግራ ኚማጋባት ይልቅ በርዕይና በፍልስፍናና ላይ ያተኮሚና፣ ደሹጃ በደሹጃ ዚህዝባቜንን ቜግር ሊፈታ ወደሚያስቜል ፖሊሲና ዚአጻጻፍ ስልትና ክርክር ማትኮር አለብን። ኹዚህ ዐይነቱ አስ቞ጋሪ ሁኔታ በመነሳት ትክክል ናቾው ብዬ ዚማምንባ቞ውን ነጥቊቜና ዚአፈታት ዘዎዎቜ በተናጠል አትታለሁ ። በመጀመሪያ ግን ዚስርዓት ጥያቄ ላይ ትንሜ እንቆይ።

 

ዚስርዓት ጥያቄ!

ስርዓት ማለት ምን ማለት ነው? ስርዓት ዹሚለውን በቀጥታ ወደ እንግሊዘኛው ሲይስተም ወደሚለው ብንተሚጉመው ዚተሻለ ስዕል እናገኛለን። እንደሚታወቀው ማንኛውም ህይወት ያለው ነገርና እራሳ቞ው አትክልቶቜም ሆነ ዛፎቜ ሁሉ በስርዓት ዚተደራጁ ና቞ው። በተወሰነ ዹአውቃቀር ስልት ዹተዘጋጁ ና቞ው። በራሳ቞ውም ውስጥ ራሳ቞ው ዚማደራጀትና ዹማደግ ውስጣዊ ኃይል አላ቞ው። ለምሳሌ ለጊዜው አንኳ ቢሆን በተፈጥሮ ውስጥ መናጋት ቢደርስ ተፈጥሮ በራሷ ውስጣዊ ኃይል በመሚጋጋት ተናግቶ ዹነበሹው ሁሉ በተፈጥሮ ራስን በራስ ዚማደራጀትና ዹማደግ ኃይል እንደገና ወደመስተካኚል ያመራል። አትክልቶቜም ሆነ ወደ ዛፍነት ዚሚለወጡት ቜግኞቜ በውስጣ቞ው ራሳ቞ውን ዚማደራጀት ኃይል ውሃንና ሚኒራሎቜን ኚመሬት ውስጥ በመምጠጥና ለዕድገታ቞ው በመጠቀም፣ በጾሀይ ጹሹር በመታገዝ ያብባሉፀ ፍሬም ይሰጣሉ። ዚመጚሚሻ መጚሚሻ ፍሬ ካላ቞ው ፍሬያ቞ውን ለቅመን ለምግብ እንጠቅምባ቞ዋልን። ፍሬ ዚማይሰጡ ዛፎቜ ኹሆኑ ደግሞ ለማገዶና ለቀት መስሪያ እንጠቅምባ቞ዋልን። ሰውነታቜንም ቢሆን ራሱን ዚቻለ ሲይስተም ያለው ወይም በስርዓት ዚተደራጀ ነው ማለት ይቻላል። ይሁንና ግን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ፣ ወይም በአንዳቜ በማይታወቅ ምክንያት ሰውነታቜን አስፈላጊውን እንክብካቀ ሲያጣ ዚሰውነታቜን ኊርጋኖቜ ወደ መናጋት ያመራሉ። ዚአጋጣሚን ነገር ወደጎን ትተን ዚእኛ በስርዓት መንቀሳቀና ማሰብ ወይም አዳዲስ ነገሮቜን መፍጠርና ለህብሚተሰባቜን አስተዋፅዖ ማድሚግ በእኛ በስነ-ስርዓት ማደግና ጭንቅላታቜን በስነ-ስርዓት መቀሚጜ ዹሚወሰን ነው። ንቃተ-ህሊናቜንም ሆነ ዚኑሮአቜንን ሁኔታ ሊወሰኑ ዚሚቜሉት ኹላይ በተጠቀሱት ነገሮቜ ሲሆን፣ አስተዳደጋቜን ዹተወሰነ እንኚን ካለበት በቀላሉ ሊወገድ በማይቜል አደጋ መጋለጥ አንቜላለን። በሌላ ወገን ግን ኹኛ ቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ በመጋለጥ ዚወደፊቱ አኗኗራቜን ሁኔታና ዚህብሚተሰብአቜን ስርዓት ዚሚናጋበትና በቀላሉ ማስተካኚል ዚማይቻልበት ሁኔታ ይፈጠራል። ያም ሆነ ይህ ለሰውነታቜንም ሆነ ለጭንቅላታቜን እንዲሁም ለማህበሚሰብ ዕድገት ዚግዎታ በስርዓት መደራጀት፣ በስርዓት መንቀሳቀስ፣ በስርዓት ስራን መስራት፣ በስርዓት እያሰቡ መነጋገርና ወደ አንዳቜ ነገር ለመድሚስ ስርዓት ዚሚባለው ነገር ወሳኝ ሚናን ይጫወታል። ስለሆነም ስርዓት ዚሚባለው ነገር ለአንድ ህበሚተሰብ ዹጉዞ አቅጣጫ ነው ብሎ መናጋር ይቻላል። በሌላ ወገን ግን ህብሚተሰብን ስርዓት ባለው መልክ ለማደራጀት ግብታዊነትም (Spontaneous) ዚሚጫወተው ሚና እንዳለ መዘንጋት ዚለብንም። አንድን ነገር በማቀድ ውስጥ ዕቅድና ግብታዊነት ጎን ለጎን ሊሄዱ እንደሚቜሉ መዘንጋት ዚለብንም።  ያም ሆነ ይህ አንድ ሰው በአንድ ህብሚተሰብ ውስጥ ሲኖር በምን ዐይነት ስርዓት ውስጥ ነው ዹምኖሹው? ብሎ ራሱን መጠዹቅ አለበት። ማንኛውም ሰው ለመኖር ብቻ ስለማይኖር ዚኑሮን ትርጉም እንዲሚዳ ኹተፈለገ ዚሚኖርበትን ሁኔታ መጠዹቅ አለበት። በስርዓት ሊያኖሚው ዚማያስቜለው ሁኔታ በስርዓት ዹተዋቀሹ ስርዓት ካልሆነም ለምን ዚተዘበራሚቀ ሁኔታ እንደተፈጠሚና ህብሚተሰብን እንደሚያዋክብ ራሱን መጠዹቅ አለበት።

በአገራቜን ዹተፈጠሹው ቜግር ስርዓት ሲባል ኚርዕዮተ-ዓለም ጋር በመያያዝ ብዙ ሰዎቜን ግራ ሲያጋባ ይታያል። በሌላ ወገን ደግሞ ዚግዎታ ሆኖ ህብሚተሰብአቜንን ስርዓት ባለው መልክ ለማደራጀት ኹተፈለገ ዚግዎታ ርዕዮተ-ዓለም በሉት ፍልስፍና ወሳኝ ሚናን ይጫወታሉ። ግልጜ ለማድሚግ፣ ህግን ወደጎን ትተን አንድ ህብሚተሰብ ለመኖር ሲል ዚግዎታ በስራ-ክፍፍል መደራጀት አለበት። ሁሉም ተመሳሳይ ነገር ስለማያመርት ይህ ዐይነቱ ዚአደሚጃጀትና ዚአመራሚት ስልት ዚግዎታ  ወደልውውጥ ያመራል። በሌላ ወገን ግን ይህ ዐይነቱ ሁኔታ ዚግዎታ በሳይንስ ላይ ወደተደራጀ ዚአሰራር ስልት ላይ ያመራናል ማለት አይደለም። ስራው ተደራራቢና አሰልቺ እንዳይሆን፣ ወይም ደግሞ አድካሚ እንዳይሆን ኹተፈለገ በሳይንሳዊ ምርምር አማካይነት ወደተሻለ ዚአደሚጃጀትና ዚአመራሚት ስርዓት መዋቀር አለበት። በዚህ አማካይነት ብቻ ነው በዹጊዜው ዚሚኚሰቱ ቜግሮቜን መፍታትና ስርዓት ያለው ኑሮ መኖር ዚሚቻለው።

እስኚዛሬ ድሚስ በብዙዎቻቜን ዘንድ ያለው አለመግባባት፣ አብዛኛዎቻቜን ኹንፁህ ርዕዮተ-ዓለም ጥላቻ በመነሳት ወይም ስርዓትን ኚርዕዮተ-ዓለም ጋር በማያያዝ ወደማያስፈልግ ሜኩቻ ውስጥ እንገባለን። ብዙዎቻቜን ለምርምር ጊዜ ስለሌለን በአንዳንድ ጮሌዎቜ በሚነፍስ ቅስቀሳ ወይም ጥላቻ በመጠመድ ቜግርን ኚመፍታት ይልቅ ቜግርን ለመፍጠር እናመራለን። ይህንን ግራ መጋባት መልክ ለማሲያዝ፣ ለመሆኑ ለምን ዐይነት ስርዓት ነው ዚምንታገለው? ዹሚለውን ጥያቂ ተቀራራቢ መልስ ለመስጠት ወይም አስታራቂ ነገር ለማቅሚብ ወደ ውይይት እናምራ።

ስለማህበራዊ ስርዓት በምናወራበት ጊዜ በማውቅም ሆነ ባለማወቅ ዚአንድን ሀብሚተሰብ ጉዞና ዕድል በገበያ ኢኮኖሚና በሶሻሊዝም መሀኹል ነው ዚምንኚልለው። ዚገበያ ኢኮኖሚ ቜግራቜንን ዚሚፈታልንና ሶሻሊዝም ደግም ጹለማዊ ስርዓትን እንደሚያጎናጜፈን አድርገን ነው ዚምንቆጥሚው። በዚህ ዐይነቱ ዚአስተሳሰብ ክልል ውስጥ ህብሚተሰብ ማለት ምን ማለት እንደሆን ዚሚታወቅ ነገር ዚለም። አንድ ህብሚተሰብም ኚገበያ ኢኮኖሚ ባሻገርና በብዙ ሺህ ድሮቜ ዚተሳሰሚ ወይም መተሳሰር እንዳለበት ግልጜ ዹሆነልን አይመስልም። ይህ ዐይነቱ በደንብ ያልተጠና አስተሳሰብ በጭንቅላታቜን ውስጥ ስለተቀሚፀ አንድን ህብሚተሰብ እንደ አንድ ወጥና፣ በሁለት አማራጭ መሀኹል ብቻ እንደሚካሄድ ትግል አድርገን  በመቁጠር ሰፋ ያለና በጥናት ላይ ዚተመሚኮዘ ውይይት እንዳይካሄድ ኚመጀመሪያውኑ ኡእሃሳብ ዕገዳ እናደርጋለን። በሌላ ወገን ግን ጊዜ ወስዶ ለሚመራመርና ለሚጜፍ በታሪክ ውስጥ አንድ ወጥ ስርዓት ዚለም። ሌላው ቢቀር ሁሉም ነገር በገንዘብ በሚለካበትና በሚተመንበት ዚካፒታሊስት ህብሚተሰብ ውስጥ ስርዓቱን እዚተቀናቀኑ ዚሚኖሩ ዚአሰራር፣ ዚአመራሚትና ዹአኹፋፈል ሁኔታዎቜ አሉ። ይህ ብቻ ሳይሆን፣ አንድ ዐይነት ኢፊሲያላዊ ዚገንዘብ መሜኚርኚርና ዚክፍያ ዘዮ ባለበት በካፒታሊስት ዚገበያ ኢኮኖሚ ውስጥ እዚያው በዚያው ጎን ለጎን ዚሚንቀሳቀስ በሎካል ደሹጃ ዚሚሜኚሚኚር ዚገንዘብ ዐይነት አለ። በሌላ አነጋገር፣ ኚዶላርና ኚኊይሮ ውጭ ሌሎቜ ዚመገበያያ ዚገንዘብ ዐይነቶቜ አሉ ማለት ነው። ይህንን ዐይነቱን ዚልውውጥና ተቀባይነት ካለው ስርዓት ውጭ ዚሚንቀሳቀስ ገንዘብ አትመው ዚሚንቀሳቀሱ ኃይሎቜ ኹፍተኛ ዕውቀት ያላ቞ውና በራሳ቞ው ዹሚተማመኑ ብቻ ና቞ው። ይህም ማለት ምን ማለት ነው? አንድን ነገር በጥቁርና በነጭ መሀኹል እዚሳልን ይህንን ወይም ያኛውን ምሚጥ እያልን ዹምንፋለም ኹሆነ ሰፋ ያለና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ እንዳይዳይዳብርና ባህልም እንዳይሆን ኚመጀመሪያውኑ እናግዳለን ማለት ነው። በተጚባጭም ዕድገት እንዳይኖር እንቅፋት እንፈጥራለን።

ያም ሆነ ይህ አንድ ህብሚተሰብ በኢኮኖሚዊ ስርዓት ብቻ ዚሚገለጜ አይደለም። ኢኮኖሚ ዹጠቅላላው ስርዓት አንድ አካልና መሰሚት ነው። ይህም ማለት አንድ ህብሚተሰብ በፖለቲካ፣ በባህል፣ በርዕዮተዓለም፣ በኢኮኖሚና በልዩ ልዩ ዹአኗኗርና አመራሚት ሁኔታዎቜ ዚሚገለጜ ነው። ኹነዚህ በስርዓቱ ውስጥ ተጠቃለው ኚሚታዩት ነገሮቜ ሁሉ ፖለቲካዊ አደሚጃጀትና ንቃተ-ህሊና ወሳኝ ሚናን ሲጫወቱ፣ ዚሌሎቜ ንዑስ ክፍሎቜ በስርዓት መስራትና መንቀሳቀስ ሊወሰን ዚሚቜለው በፖለቲካው ስርዓትና አደሚጃጀት፣ እንዲሁም ዹንቃተ-ህሊና ዚዕድገት ደሹጃ ነው። ፖለቲካዊ አወቃቀር ጀናማ በሆነበት ህብሚተሰብና፣ በኹፍተኛ ንቃተ-ህሊና ፖሊሲዎቜ በሚነደፉበት ህብሚተሰብ ውስጥ ዚሌሎቜ ንዑስ ክፍሎቜ ዕድገትና መዳበር መልክ ይይዛል። ሌሎቜ ንዑስ ክፍሎቜ ይፋፋሉፀ ያድጋሉ።  ይህም ማለት በማንኛውም ህብሚተሰብ ውስጥ ዚሌሎቜ ንዑስ ክፍሎቜ ማደግና ሚናቾውን መጫወት ዚግዎታ በፖለቲካዊ ንቃተ-ህሊናና አደሚጃጀት ዹሚወሰን ነው። በተጚማሪም ኚፖለቲካዊ አደሚጃጀት ባሻገር በዚአንዳንዱ ንዑስ-ክፍል ውስጥ ያሉ ኃይሎቜ አንደኛው በሌላው ላይ ተፅዕኖ በማድሚግ አንዱ ዹሌላውን ዕድገት ይወስናል። ይህም ማለት ማንኛውም ንዑስ-ክፍል በራሱ ብቻውን ዹሚጓዝ አይደለም ማለት ነው። በተለይም አሁን ባለንበት ነገሮቜን ነጣጥሎ በሚታይበትና፣ ዚፖለቲካን ጉዳይ ለጥቂት ፖለቲኚኛ ነን ባዮቜ በተጣለበትና በሚጣልበት ኢምፔሪሲስታዊና ዚሶፊስቶቜ ዓለም ውስጥ ፖለቲካና ፍልስፍና፣ ፖለቲካና ኢኮኖሚ፣ ፖለቲካና ህብሚተሰብ እዚተነጣጠሉ በመታዚት ፖለቲካ ሳይንሳዊና ምሁራዊ ባህርዩን እያጣ በመምጣት ጥቂት ሰዎቜ እንደፈለጋ቞ው ዚሚፈነጩበት፣ ማህበሚሰቊቜ ሹጋ ብለውና ጥበባዊ በሆነ መልክ እንዳይደራጁና፣ አንድ ህዝብ ዘለዓለሙን እዚተሚበሞ እንዲኖር ዚማድሚግ አዝማሚያ በጉልህ ይታያል። ብዙ አገሮቜ ወደ ጊርነት እያመሩ ነው። እጅግ አስ቞ጋሪ ዓለም ውስጥ ነን ያለነው ማለት ነው።

ይህ ዐይነቱ ዚአመለካኚት ቜግር ዹሚመነጹው ኹምን ዚተነሳ ነው?  ዚብዙዎቻቜን ቜግር ለምሳሌ ዛሬ በዓለም አቀፍ ዹተሰፋፋውን ዚግሎባል ካፒታሊዝምና ዚገበያ ኢኮኖሚ ዕድገት ደሹጃ ዚታሪክ ሂደት ውጀት መሆኑን ለመቀበል አለመፈለግ ነው ። ኹዚህም በመነሳት ይህ ስርዓት ድሮም ዹነበሹና ወደፊትም ዚሚኖር፣ ዚመጚሚሻው ዹሰው ልጅም ዕጣ ኚሱ ጋር ዚተሳሰሚ አድርጎ ኚመወሰድ ዚተነሳ ኢ-ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ዹመነጹ ነው ብል እንደ ስድብ እንደማይቆጠርብኝ ተስፋ አደርጋለሁ። ስለሆነም ሁሉም አገሮቜና ህብሚተሰቊቜ፣ ኚታሪካ቞ውና ኚባህላ቞ው፣ እንዲሁም ኚልምዳ቞ውና ኚህብሚተሰብአ቞ው ባሻገር መቀበል ያለባ቞ው ስርዓት ነው። ይህ ዐይነቱ አጉል ውስንና አደገኛ አስተሳሰብ ህብሚተሰብአቜን ኹሚፈልገውና ኚሚጠብቀው ስርዓትና ኚተጚባጩ ዚህብሚተሰብ ሁኔታ ጋር ሊጣጣም ዚሚቜል አይደለም። ምክንያቱም ይህ ዐይነቱ አደገኛ አመለካኚት ጥቂት ኢሊት ነን ባዮቜ ሳያወጡ ሳያወርዱ በህብሚተሰብአቜን ላይ ዚሚጭኑት ስርዓት ስለሆነና ስለሚሆን ህብሚተሰብአቜን ዹሚፈልገውን ነገር በፍጹም ሊያገኝ አይቜልም።

ለምሳሌ ዚካፒታሊዝምን ስርዓት ስንመለኚት ቀድሞውኑ ታቅዶና ተፈልጎ ዹተዋቀሹ ስርዓት አይደለም። በታሪክ ሂደት ውስጥ ዹተፈጠሹና በተወሰነ አካባቢ ብቻ ሊዳብርና ሊስፋፋ ዚቻለ ነው። ስለካፒታሊዝም ስርዓት በምናወራበት ጊዜ ስርዓቱ እንደማህበራዊና እንደ ኢኮኖሚያዊ ቅንጅትና ክንዋኔ ዚዛሬውን መልክ ኚመያዙ በፊት ዚምዕራብ አውሮፓ ህዝብ በአጋጣሚ ባገኘው ዕውቀት ሬናሳንስ ዚሚባለውን ዚጭንቅላትና ዚመንፈስ ተሃድሶ በማድሚግና በአዲስ ዕውቀት በመመራት ሰዎቜ ዚማሰብ ኃይላቾውን ተጠቅመው ዚታሪክ ባላቀት እንዲሆኑ መንገዱ ይቀደዳል። ይህም ማለት ዚአውሮፓው ካፒታሊዝም ካለሪናሳንስ ወይም ካለመንፈስ ተሃድሶ ውጭ በፍጹም ሊታስብ ዚሚቜል አይደለም። ይህ አዲስ ዹተፈጠሹው ሁኔታ ለኚተማዎቜ ዕድገት፣ ለዕደ-ጥበብ ማበብና ለንግድ መስፋፋት መንገዱን ይጠርጋል። በተለይም በሩቅ ንግድ አማካይነት ዚገንዘብ ሀብት ማኚማ቞ት ዚቻለው ነጋዮ ዚሞናርኪዎቜን ጊርነት ፋይናንስ ዚሚያደርግና፣ በተለይም ደግሞ ዹዕደ-ጥበብ ሙያን ወይም ዹጎጆ ኢንዱስትሪዎቜን ቀስ በቀስ በቁጥጥሩ ስር በማድሚግና አዳዲስ ምርቶቜ እንዲመሚቱ ትዕዛዝ በመስጠትና ለገበያ በማቅሚብ(Putting-Out system) አዲስ ዚፍጆታ አጠቃቀም ባህል እንዲዳብር አደሚገ።  ይህ በራሱ ደግሞ አዲስ ምሁራዊ እንቅስቃሎ እንዲዳብርና በጊዜው ዹነበሹውን ፊዩዳላዊ አስተሳሰብ ጋር እንዲጋጭ ያደርገዋል። በ14ኛውና በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ዹተጀመሹው ዚድሮውን ቀኖናዊ አስተሳሰብ መቀናቀንና፣ አዳዲስ ዚአስተሳሰብ ፈለጎቜን መቅደድ አዲስ ኹተፈጠሹው ሁኔታ ጋር ዚተያያዘ ነው። ይህ ብቻ አልበቃም። ዚአውሮፓውም ማህበሚሰብ፣ በተለይም ዚካቶሊክ ሃይማኖት በጣም ዹጠበቀ አስተሳሰብ ዹነበሹውና ጹቋኝ ስለነበር እሱን ዚሚጋፈጥ በማርቲን ሉተር አማካይነት ዚሃይማኖት ተሃድሶ እንቅስቃሎ ማካሄድ አስፈለገ። ይህ በራሱ ማክስ ቬበር እንደሚለው ለአዲስ አስተሳሰብ ሁኔታውን በማመቻ቞ት ዚፕሮ቎ስታንት ስነ-ምግባር ዚሚባለው ዚስራና ሀብትን ዚማካበት ልምድ በመዳበሩ ለካፒታሊዝም ዕድገት ሌላ ዕምርታ ሰጠው። ይሁንና ግን ካፒታሊዝም በአሞናፊነት እንዲወጣ ሌላ እንቅስቃሎ መካሄድ ነበሚበት። ዚአውሮፓውን ማህበሚሰብ ኚፍጹም ሞናርኪዎቜ አምባገነናዊ አገዛዝ አላቆ ርፑብሊኮቜን ማቋቋም አስፈላጊ ሆነ። ይኾኛው እንቅስቃሎ በኢንላይትሜንት ወይንም በተገለጞለት ምህራዊ እንቅስቃሎ ዹሚወኹልና ለሊበራሊዝም አስተሳሰብ መስፋፋት በሩን ዹኹፈተ ነው። ኹዚህ ጋር በመያያዝ መሬት ዹግል ሀብት መሆን፣ ይህ ጉዳይ ኹህግ ዚበላይነት ጋር መያያዝ ለካፒታሊዝም መሰሚት ሆነ። ይህ በዚኀፖኩ ዹተፈጠሹው አዳዲስ ሁኔታ ለመጚሚሻ ጊዜ ዚፊዩዳሉን ስርዓት በማስወገድ ካፒታሊዝም በአሞናፊነት መውጣት ቻለ። ዚአውሮፓው ማህበሚሰብም ዕድል ኚእንግዲህ ወዲያ በካፒታሊዝም ምርታዊ እንቅስቃሎና ውስጠ-ኃይል ዹሚወሰን ሆነ። ይህ ጉዳይ እንደስርዓት በመወሰድና ተቀባይነት በማግኘት ህብሚተሰቡ በዚህ ዚሚንቀሳቀስ ሆነ። በዚህ መልክ ዛሬ ካፒታሊዝም ዚሚባለውን ስርዓት እንድናይና፣ እንድንኖርበትና እንድንጠቀምበት ተገደድን። ይህ ስርዓት በአስተሳሰብ ስልት(Mode of thought)፣ በአመራሚት ስልት(Mode of production)፣ በምርት ግኑኝነት(Production relationship)፣ በርዕዮተ-ዓለማዊና በባህላዊ(Mode of consumption and behaviour)  ዚሚገለጜና፣ ግለሰባዊ ድርጊትነትና ማንነት ዚተሚጋገበጥ ስርዓት ነው። ለምን በሌሎቜ አገሮቜ ውስጥ እንደዚህ ዐይነቱ ስርዓት ሊፈጠር አልቻለም ለሚለው መልስ ለመስጠት በጣም አስ቞ጋሪ ነው። ይሁንና ግን እኛ ስለስርዓት በምንታገልበት ጊዜ ኹምን ተነስተና ወዎት እንደምንጓዝና፣ ምን ምን ቜግሮቜ ኚፊታቜን ተደቅነው አስ቞ጋሪ ሁኔታ እንደሚፈጥሩብን ግንዛቀ ማግኘት እንቜላለን። በሌላ ወገን ግን ዚታሪክን ሂደትና አስቜጋሪ ጉዞ ሳይጠና እንዲያው በአቊሰጡኝ ተግባራዊ ዹሚሆን ስርዓት እንበለው ፖሊሲ ወደ መቀመቅ ውስጥ ይኚተናል። አብዛኛዎቜ ህብሚተሰቊቜንም እዚኚተታ቞ው ነው። ስለሆነም ስለ ስርዓት ወይም ስለማህበሚሰብ ግንባታ በምናወራበት ጊዜ በቲዎሪና በኢምፔሪካል ደሹጃ ማጥናት ያሉብን መዓት ነገሮቜ አሉ ማለት ነው። ዚፊዩዳሉን ስርዓት ወደ ካፒታሊዝም እንዎት እንደተሞጋገሚ ለመገንዘብ ኚታቜ ዹቀሹበውን ስዕል መመልኚቱ ነገሩን ዹበለጠ ግልጜ ያደርገዋል።

 

 

 

 

 

ዚካፒታሊዝም ጉዞና ዚዕድገት ደሚጃ፣ እንዲሁም በዚኀፖኩ ያጋጠሙትን ቜግሮቜ በደንብ ኹመሹመርንና ግንዛቀ ውስጥ ካስገባን አንድን ማህበሚሰብ ለማደራጀት ቀላል ይሆንልናል። ደሹጃ በደሹጃ መወሰድ ያለባ቞ውን ነገሮቜ ተግባራዊ ለማድሚግና ህብሚተሰብአቜንን መልክ ለማስያዝ ይቀለናል። ዛሬ በአገራቜንም ሆነ በአብዛኛዎቜ ዚሶስተኛው ዓለም አገሮቜ ያለው ቜግር ስለካፒታሊዝም ዕድገት ያላ቞ው ግንዛቀና በምን ውስጣዊ ህግ እንደሚተዳደር ግራ መጋባት ህብሚተሰቊቻ቞ውን እያተሚማመሰባ቞ው ነው። ኚፊዩዳሊዝም አስተሳሰብ ሳይላቀቁ ሶሻሊዝምንና ዚሊበራል ካፒታሊዝምን ስርዓት ተግባራዊ ለማድሚግ መሯሯጥ፣ ህብሚተሰቊቜ መስራት ያለባ቞ውን ነገሮቜ እንዳይሰሩና እንዳይገነቡ በመታገድ ህዝቊቜ በስርዓት እንዳይኖሩ እያደሚገ ነው። በተለይም ዛሬ ዹተፈጠሹው ውስን አስተሳሰብ፣ ካለሊበራል ዲሞክራሲና ካለገበያ ኢኮኖሚ ሌላ አማራጭ ዹለም እዚተባለ ዹሚሰበኹው አደገኛ ቅስቀሳ ደሃ ዹሆነውን ሰፊ ህዝብ መኖሪያ እያሳጣው ነው። በአገሩ ሰርቶ እንዳይኖር እያደሚገው ነው። ህዝቊቜ በአገራ቞ው ውስጥ ህልማቾውን ዕውን እንዳያደርጉ ሁኔታው ሁሉ ጚልሞባ቞ዋል። ስለሆነም ኚፊታቜን አስ቞ጋሪ ነገር ተደንቅሮ ይገኛል ማለት ነው።

ይህንና በአጠቃላይ ሲታይ አሁንም ቢሆን አንድን ህብሚተሰብ በአንድ ዚስርዓት ክልልና አመለካኚት ብቻ ልናደራጀው በፍጹም አንቜልም። ብዙ ስርዓቶቜ አንድ ላይ ተቀነባብሚው ሊሄዱ እንደሚቜሉ መገንዘብ ይኖርብናል። በሌላ ወገን ግን ይህ ሆነ ያኛው ስርዓት ዚግዎታ መታቀድ አለባ቞ው። ካለዕቅድ ዚሚሰራ ነገር ዚለም። ዹለም ይህ አያስፈልግም ዹምንል ኹሆነ ደግሞ በቀጥታ ወደ ስርዓተ-አልበኝነት ነው ዚምናመራው ነው።  በአሁኑ በግሎባላይዜሜን ዘመን ሁሉ ነገር ልቅ መሆን አለበት፣ አገሮቜ ድንበሮቻ቞ውን ማጠር ዚለባ቞ውምፀ ለዓለም ዚገበያ ተዋናዮቜ ገበያ቞ውን ልቅ ማድሚግ አለባ቞ው እዚተባለ በሚሰበክበት ዓለም ውስጥ በተለይም እንደኛ ዚመሳሰሉሉ አገሮቜ ህዝባ቞ውን በስርዓት እንዳያደራጁ ሁሉ ነገር ታጥሮባ቞ዋል። በተለይም ኢንቬስተር ነን በሚሉና አማካሪዎቜ(Consulting Companys) ነን ብለው እዚህና እዚያ በመራወጥ ደካማ መንግስታትንና በጥሩ ዕውቀት ያልተገነቡ ፖለቲኚኛ ነን ባዮቜን ዚሚያታልሉ በብዛት በተሰራጩብት ዓለም ውስጥ፣ አንድን አገር በስርዓት ማዘጋጅት፣ ምርታማና ፈጣሪ ለማድሚግ እጅግ አስ቞ጋሪ ሁኔታ ይታያል። ራሱ በዕድርና በዕቁብ መደራጀት ኚሶሻሊዝም ጋር በሚገናኝበትና እንደመጥፎ ነገር በሚወሰድበት ዹኒዎ-ሊበራሊዝም ዓለም ውስጥ ሁሉም ነገር ካለ ዕቅድና ካለስርዓት ልቅ በሆነ መልክ ብቻ ነው መስራት ያለበት። ይህ ዐይነቱ፣ ሀቀኛውንና ሳይንሳዊ ዚአሰራርና ተፈጥሮአዊ ህግን ዹሚቀናቀን ልቅ ዚገበያ ኢኮኖሚ አመለካኚት በተስፋፋበት ዓለም ውስጥ ራሱ ምሁር ነኝ ዹሚለው ጥያቄ መጠዹቅ ተስኖት አሁንም ዚገበያ ኢኮኖሚ እያለ ሲጮህ ይሰማል።

አብዛኛው ታጋይ ወይም ምሁር ባይ፣ ወይም ለአገሬ እቆሚቆራለሁ ዹሚለውና እዚህና እዚያ ዚሚጮኞው በወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ በአለፉት ሃያ ሰባት ዐመታት በአገራቜን ምድር ዹተዘሹጋውን ስርዓት ለመመርመር ተስኖት ዹሚሆን ዹማይሆን ኚሳይንስ ጋር ዚማይጣጣም ነገር ሲናገር ይሰማል። ኹማንኛውም ታጋይ ወይም ምሁር ባይ በአገራቜን ምድር ውስጥ ምን ዐይነት ስርዓት እንደተዘሚጋ ዹተሰጠ መግለጫ በፍጹም ዚለም። ነገሮቜ ሁሉ በፖለቲካ ክልልና ኚስልጣን ጋር ተያይዘው ይታዩ ስለነበር በህዝባቜን ላይና በጠቅላላው ዚህብሚተሰብአቜን አወቃቀርና አሚማመድ ላይ ዹተዘሹጋው መጥፎ ስርዓት ለወደፊቷ አዲሲቷ ኢትዮጵያ ዚመገንባት ጉዳይ ዚቱን ያህል ዕንቅፋት እንደነበርና እንደሚሆን ግንዛቀ ውስጥ ዚተገባ አይደለም። ዚዛሬይቱ ኢትዮጵያ በግሎባል ካፒታሊዝም ስር ዚወደቀቜና ዚምትታሜ፣ እንዲሁም ሀብቷ ዚሚዘሚፍባት አገር ነቜ። ልክ በቅኝ ግዛት ዚአስተዳደር ዘመን በሚመስል ህዝቊቿ ወደ ባርነት ስራ ዚተሰማሩባት ሁኔታ በአንዳንድ ቊታዎቜ በግልጜ ይታያሉ። ዚሰሊጥ ተኹላ መስፋፋት፣ ዚሞንኮራ አደጋ በብዛት ተተክሎ ስኳር ማምሚት፣ ዚአበባ ተኹላና ዚቡና ምርት ልዩ ዐይነት ዚገበያ ልውውጥ ተቋቁሞ ዚህዝቡ አትኩሮ በዚያው ላይ ተወስኖ እንዲቀር ማድሚግ፣ ዚግሎባል ካፒታሊዝም ካዋቀሚው አዲስ ሁኔታ ጋር ዚተያያዘ ነው። በግሎባል ካፒታሊዝም ስትራ቎ጂ እንደኛ ያሉ አገሮቜ ወደ ፕላን቎ሜን ኢኮኖሚ(Plantation Economy) መለወጥ አለባ቞ው። ህዝባቜን ፍራፍሬ እዚተኚለ፣ ሜንኮራ አገዳና ሌሎቜ ዚእርሻ ምርቶቜን እያለማና አያስፋፋ ዚኢንዱስትሪ አገሮቜን መመገብ አለበት። በዚህ አዲሱ ስትራ቎ጂ መሰሚት እንደ ኢትዮጵያ ያሉ አገሮቜ በምንም ዐይነት በሳይንስና በቮክኖሎጂ ላይ ዹተመሰሹተ ሰፋ ያለ በኢንዱስትሪ ዚሚንቀሳቀስ ዚውስጥ ገበያ መገንባት ዚለባ቞ውም። ውብ ውብ ኚተማዎቜን በመገንባትና፣ በልዩ ልዩ ዹመገናኛና ዚመመላሻ ዘዎዎቜ በማገናኘት ህዝቊቿ ተደስተውና እንደ አንድ ህዝብ እጅ ለእጅ ተያይዘው መኖር ዚለባ቞ውም። ይህ ዐይነቱ ህብሚተሰብአዊ አወቃቀርና ዹአገር ግንባታ ለዘሹፋና አንድን ህዝብ አደኜይቶ መኖር ስለማያመቜ ግሎባል ካፒታሊዝም እንደ ኢትዮጵያ ዚመሳሰሉ አገሮቜ እዚታሹና ፍርፋሪ እዚተወሚወሚላ቞ው መኖር እንዳለባ቞ው ወስኗል። በዚህ መልክ በወያኔ አገዛዝና በግሎባል ካፒታሊዝም መሀኹል በተመሰሹተው ያልተቀደሰ ጋብቻ ህዝባቜን ዘለዓለሙን በድህነት እንዲኖር ተሚግሟል። ዛሬም ይህ ዐይኑነቱ ሁኔታ ቀትሏል። ዹዚህ ሁሉ መግለጫው ደግሞ በአገሪቱ ኚተማዎቜ ውስጥ ዚቆሻሻ ዕቃና ልብስ መሞጫ ቊታዎቜ መስፋፋት ነው። ይህ ዐይነቱ ዚቆሻሻ ዚሞቀጥ ማራገፊያ፣ ኚቻይና ዚሚመጣ በርካሜ ጉልበት ዹተመሹተ ልብስና ጫማ፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ ዚቁሳቁስ ነገሮቜ መሞጥና ዚአገሪቱ ዚኢንዱስትሪ ምርት እንቅስቃሎ መዳኚምና፣ ምርታማ ወዳልሆነና ዚማባዛት ኃይል ወደሌለው ዚምርት እንቅስቃሎ ላይ መሰማራት፣ ዚአገልግሎት መስኩ ኹፍተኛውን ቊታ መያዝና ህብሚተሰቡን ማዘበራሚቅ ዚስርዓቱ ልዩ ባህርዮቜና መግለጫዎቜ ና቞ው። ኹዚህ ስንነሳ ዹአገዛዙ ርዕይ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ዚሚገለጜ ሳይሆን፣ ግራ ዚገባው ግን ደግሞ በዘሹፋ ላይ ተመስርቶ ዚህብሚተሰቡን ውስጣዊ-ኃይልና አንዳንድ ታታሪ ሰዎቜን ዚሚጋፈጥና ለውጭ ገበያ ልቅ አድርጎ ዚህብሚተሰብአቜንን ዚማምሚት ኃይል ዚሚያዳክም ነው። በሌላ አነጋገር፣ ዚዛሬውን ዚኢትዮጵያ ዚማህበሚሰብ አወቃቀር በአንድ በጠራ አመለካኚትና አገላለጜ መግልጜና መተንተን ያስ቞ግራል። እንደዚህ ዐይነት ስርዓት ነው በአገራቜን ምድር ዹሰፈነው ብሎ መናገር ያዳግታል።  ይሁንና ግን ዚተዘበራሚቀና ወዎት እንደሚያመራ ግልጜ ያልሆነ ሁኔታ በጉልህ ይታያል።

ኹዚህ በመነሳት እዚህም ሆነ እዚያ ተደራጅቶ እታገላለሁ ዹሚለው ኃይል ሁሉ ለምን ዐይነት ስርዓት እንደሚታገል ቢያስታውቅ ለመኚራኚርም ሆነ፣ ለመማርና ለማስተማር መንገዱ ክፍት ይሆናል። ዹለም ዝምብለህ አፍህን ዘግተህ ተቀመጥ፣ እኛ ስልጣን ስንይዝ ዚዚያን ጊዜ ለምን ስርዓት እንደምንታገል በተግባር እናሳይሃለን ዚሚባል ኹሆነ ይህ ዐይነቱ አካሄድ እጅግ አደገኛና ዚጮሌዎቜ ጉዞ ነው። ለኛ ለነቃን ኃይሎቜ ግን እንደዚህ ዐይነቱ ዚጮሌዎቜ አካሄድ አይጥመንምፀ ዝም ብለንም እጃቜንን አጣጥፈን በመቀመጥ ህብሚተሰብአቜን ወደመቀመቅ ውስጥ ሲገባ ማዚት አንቜልም። ህሊናቜንም አይፈቅድም። ፊደል ዹቆጠርን ስለሆንና ዚታሪክም ኃላፊነት ስላለብን ለምን ዐይነት ስርዓት ነው ዚምትታገሉት? እያልን ኚመወትወት በስተቀር ሌላ አማራጭ ዚለንም። በመሆኑም ሁሉንም፣ ለብሄሚ-ሰብ ነፃነትም ሆነ ዚብሄራዊ አጀንዳ አለን ብለው ዚሚታገሉትን ኃይሎቜ ለምን ዐይነት ስርዓት እንደሚታገሉ ቢያስሚዱንና ግልጜ ቢያደርጉሉን ዚትግል አቅጣጫው መስመር ይይዛል ብዬ እገምታለሁ።

ያም ሆነ ይህ በጭንቅላታቜን ውስጥ አንዳቜ ዐይነት ስዕል እንዲኖሚን ኹዚህ በታቜ ያሉትን ግራፊኮቜ መመልኚቱ አንድ ህብሚተሰብ በምን መልክ መደራጀት አለበት ለሚለው ተቀራራቢ መልስ ሊሰጠን ይቜላል። ይሁንና ግን እዚህ ላይ በግራፊኩ ውስጥ እንደ ዚሀብት ቁጥጥር ጉዳይንና ክፍፍልን ዚመሳሰሉት አልተካተቱም።

ህብሚተሰብ እንደኔት-ወርክ

 

 

አንድ ህብሚተሰብ እርስ በራሳ቞ው በሚደጋገፉ ንዑስ-ስርዓቶቜ ተዋቅሮ ዚሚካሄድ ነው። አንደኛው ሌላውን ስለሚፈልገው አንደኛው በሌላው ላይ ጭነት አደርጋለሁ ቢል መዛባትና መዘበራርቅ ይፈጠራል። በተለይም በዚህ ሂራርኪ በሚመስል ዚህብሚተሰብ አወቃቀር ውስጥ ፖለቲካዊ አወቃቀር ኹፍተኛውን ቊታ ይይዛል። ዚፖለቲካው ስርዓት በዕውቅና በዕውቀት ላይ ያልተመሰሚተና፣ እንዲሁም ደግሞ ኹፍተኛ ንቃተ-ህሊና ባላ቞ው ሰዎቜ ዚማይመራ ኹሆነ ሌሎቜ ንዑስ ክፍሎቜ በስነስርዓት ሊደራጁና ህብሚተሰቡ እንደማህበሚሰብና እንደህብሚተሰብ ሊደራጅና ታሪካዊ ስራዎቜን ሊያኚናውን በፍጹም አይቜልም። ስለሆነም ስለአንድ ስርዓት ወይም ህብሚተሰብአዊ አወቃቀር በምናወራበት ጊዜ ዚግዎታ ዚፖለቲካውን መስክ ማስተካኚል ያሰፈልጋል። „አሳ መግማት ዹሚጀምሹው ኚጭንቅላቱ ነው“  እንደሚባለው አነጋገር፣ ዹተበላሾ ዚፖለቲካ ስርዓት ለዕድገት አያመቜም። ኹዚህ በመነሳት ነው ሌሎቜ ነገሮቜን ደሹጃ በደሹጃ ማደራጀትና እንደዚአስፈላጊነታ቞ው ማስተካኚል ዚሚቻለው። ስለሆነም ምን ዐይነት ፖለቲካና ምን ዐይነት አደሚጃጀት ዚህብሚተሰብአቜንን ቜግር ሊፈታው ይቜላል? ዹሚለውን ጥያቄ ለመመለስ እንሞክር።

ዚፖለቲካ አደሚጃጀትና ትርጉም ጉዳይ!

አንድ በሁላቜንም ጭንቅላት ውስጥ ዹተቀሹፀና እንደፎርሙላ ዹተወሰደ አነጋገር አለ። ይኾውም ዚግዎታ ዚመደብለ-ፓርቲ ስርዓት መኖርና፣ በዚአራት ዐመቱ ምርጫ ማድሚግ ለአገራቜን መፍትሄ ሊሆን ይቜላል ተብሎ ታምኗል። እንደሚታወቀው ዚአገራቜን ቜግር ውስብስብ ነው። ኢኮኖሚው ዚተዘበራሚቀና ህብሚተሰብአቜንን ሊመግብና ለህዝባቜን አለኝታ ሊሆን ዚሚቜል አይደለም። ዚባህሉም ሆነ ሌሎቜ ማህበራዊ ነገሮቜ በደንብ ዚተደራጁ አይደሉም። ይህ ዋናው መሰሚታዊ አስ቞ጋሪ ጉዳይ ሲሆን፣ ባለፉት ሃያ ሰምንት ዐመታት በተለይም ኮሙኒዝም ዚሚባለው ስርዓት ኚፈራሚሰ በኋላ በምስራቅ አውሮፓ ይኾኛውን ወይም ያኛውን ርዕዮተ-ዓለም እንኚተላለን ዹሚሉ ፓርቲዎቜ እንደ አሾን በፈለቁበትና ዚፖለቲካ ተዋናዮቜ በሆኑበት አገሮቜ ፓርቲዎቹ በደንብ አለመደራጀታ቞ው ብቻ ሳይሆን ስልጣን ላይ በሚወጡበት ጊዜ ህብሚተሰቊቻ቞ውን ዚባሰውን ሲያዘበራርቁ ይታያል። አብዛኛዎቹም በራሳ቞ው ኃይል ዚሚንቀሳቀሱ ሳይሆኑ ዹዚህ ወይም ዚዚያኛው ኃያል መንግስት ትዕዛዝ ተቀባይ በመሆን ቜግር ፈቺዎቜ ኹመሆን ይልቅ ቜግር ፈጣሪዎቜ ሆነዋል። አንዳንዶቹ ወደማፊያነት ዚተለወጡ ነው ዚሚመስለው። ቡልጋሪያንና ሩሜኒያን መመለክቱ ጥሩ ግንዛቀ ሊሰጠን ይቜላል። በዚህም ዚተነሳ እነዚህም ህዝቊቜም ሆነ አብዛኛዎቹ ዚአፍሪካ ህዝቊቜ ዚዚፓርቲዎቜና አገዛዝ ነን በሚሉ ቁራኛ ውስጥ ወድቀዋል።ህዝቊቜ ዚዚአገሮቻ቞ው ባይተዋር በመሆን ዝምብለው እንዲመለኚቱ ተገደዋል። በመሆኑም በእነዚህ ዚድሮ ምስራቅ አውሮፓ ዚኮሙኒስት አገሮቜ ተግባራዊ ዹሆነው ዚገበያ ኢኮኖሚ ድህነትን ፈልፋይ ኹመሆን በስተቀር ያመጣው ፋይዳ ነገር ዚለም።

ይህ ቜግር ኹምን ዹመነጹ ነው? እንደ አገራቜን ሁኔታም ዚእነዚህ አገሮቜ መሰሚታዊ ቜግር በሬናሳንስና በኢንላይትሜንት እንቅስቃሎ ውስጥ ስላላለፉ ኚውስጥ ህብሚተሰቡን ሊመራ ዚሚቜል ምሁራዊ ኃይል ሊፈልቅና ሊዳብር አልቻለም። ኚበር቎ያዊ ዹሆነ ህብሚተሰብአዊ አወቃቀርና በካፒታሊዝም ሎጂክ ላይ ዚተገነባ ኢኮኖሚም መፈጠር ስላልቻለ ብስለትና ጥበብ ዚተሞላበት ፓለቲካ ማካሄድ ዚማይቜሉበት ሁኔታ ሊፈጠር ቻለ። ስለሆነም በአገራቜን እንደሚታዚው ዐይነት በነዚህም አገሮቜ ውስጥ ኹፍተኛ ምሁራዊ ክፍተትና ዚመደባዊ አደሚጃጀትና ዕድገት ቜግር በጉልህ ይታያል። ስለዚህም አብዛኛዎቹ ፓርቲዎቜ አንድ ዚፖለቲካ ድርጅት ማድሚግ ያለበትን መንሳቀሻ መሰሹተ-ሃሳቊቜ ያሟሉ አይደሉም። ብዙዎቹም ይህንን ወይም ያኛውን ዚፓርቲ ስም ቢይዙም ለምን ይህንን ወይም ያኛውን ስም እንደመሚጡም ዚሚያውቁ ዚሚመስሉ አይደሉም። ዚሶሻል ዲሞክራቲክ ፕሮግራም ይዞ ዚሚንቀሳቀሰው ምርጫ አሾንፎ ስልጣን በሚይዝበት ጊዜ ዕልም ያለ ዹኒዎ-ሊበራል ዚኢኮኖሚ ፖሊሲ ሲያራምድ ይታያል። ህዝቡን ዚባሰውን ወደድህነት ይገፈትሚዋል። በዚህም ምክንያት ዚድሮዎቹ ዚምስራቅ አውሮፓ አገሮቜ ዚፖለቲካና ዚኢኮኖሚ ሁኔታ ያልተሚጋጋና ህዝቊቜን ዚስራ መስክ ዕድል መስጠት ያልቻለ ነው። አብዛኛዎቹ ዚምስራቅ አውሮፓ አገሮቜ አገዛዞቜ በራሳ቞ው ማድሚግ ዚሚገባ቞ውንና ዚሚቜሉትን ማድሚግ ተስኗ቞ው ዚአውሮፓው አንድነት ዹኒዎ-ሊበራል ፖሊሲ መጫወቻ ሆነዋል ማለት ይቻላል።

ወደ አገራቜንም ስንመጣ ያለው ቜግር ይህንን ይመስላል። አብዛኛዎቹ ድርጅቶቜ ኚፕሮግራም አልፈው ዚሄዱና ዚሚሄዱ አይደሉም። ዚፖለቲካና ዚኢኮኖሚ ፍልስፍና቞ውም ግልጜ አይደለም። በዚህም ምክንያት ለምን ዐይነት ህብሚተሰብ እንደሚታገሉ ግልጜ አይደለም። እንዲያው በደፈናው ሁሉም ለገበያ ኢኮኖሚ ዚሚታገልና ጥብቅና ዹቆመ ነው ዚሚመስለው። ዚገበያው ኢኮኖሚ ደግሞ በምን መልክ መዋቀር እንዳለበትና፣ እንዎትስ ደሹጃ በደራጃ ዚህብሚተሰብአቜንን ቜግር እንደሚፈታ ግልጜ ሆኖ አልቀሚበም።

በእኔ ዕምነትና ምርምር ብዙዎቜ በፓርቲ ደሹጃ ተደራጀን ዚሚሉት በምሁራዊ ክንዋኔና ዹክርክር ሂደት ውስጥ አልፈው ዚተዋቀሩ አይደሉም። ይህም ማለት በኢትዮጵያ ውስጥ ዚሚታዚው ኹፍተኛ ዚፖለቲካ ክፍተትና ዚተዘበራሚቀ ዚህብሚተሰብ አወቃቀር ውጀቶቜ እንጅ በዕምነትና በርዕይ ዙሪያ ኚሚዥም ጊዜ ክርክርና ጥናት በኋላ ዹተቋቋሙ አይደሉም። ዚትቜትን ባህልና ነገሮቜን ኹሁሉም አንፃር ግንዛቀ ውስጥ አስገብቶ ዚመኚራኚር ልምድ ዚላ቞ውም። በዚህም ምክንያት አንድኛው በአጋጣሚም ሆነ በምርጫ ስልጣን ላይ በሚወጣበት ጊዜ ዚህብሚተሰብአቜንን ዚተወሳሰበ ቜግር ለመፍታት እንደሚሳነው ኹአሁኑ አፍን ሞልቶ መናገር ይቻላል። ሌላው ዚእነዚህ በአገራቜን እንቀሳቀሳለን ዹሚሉ ድርጅቶቜ ቜግር በብሄራዊ ነፃነታቜን ላይና፣ በጠቅላላው ስለዓለም ፓለቲካና ዚኢኮኖሚ አወቃቀር ያላ቞ው ግንዛቀ ግልጜ አይደለም። ንቃተ-ህሊናቾው በጣም ዝቅተኛ ኹመሆኑ ዚተነሳ በዓለም አቀፍ ደሹጃ ምን እንደሚካሄድ በፍጹም ዚሚያውቁት ነገር ዚለም።

አብዛኛዎቹ ዹዓለምን ዚተወሳሰበ ዚፖለቲካ ሁኔታ በዚዋህነት መነፅር ነው ዚሚመለኚቱ እንጂ፣ በምሁራዊ ትንተናና ግንዛቀ ቀሚብ ብለው በመመልኚት ምን ምን ዐይነት ፖለቲካ መኹተል እንዳለባ቞ው ዚተሚዱ አይመስሉም። ብዙዎቹ ፓርቲዎቜ ዚራሳ቞ው ዹሆነ ኢንስቲቱሜንና፣ ዚፖለቲካና ዚኢኮኖሚ እንዲሁም ዚልዩ ልዩ ዘርፎቜ አማካሪዎቜ ያሏ቞ው አይመስልም። ይህ ዐይነቱ ዚአደሚጃጀት ባህልና ዚኀክስፐርቶቜ ስራ ባለመኖሩ፣ ስራ቞ውና ፖለቲካዊ አሚማመዳ቞ው ግብታዊ ነው። ኹሌላ ዚሚመጣ ገንቢ ዹሆነ ትቜታዊ አቀራሚብና መፍትሄን ለመቀበል ዹተዘጋጁ አይደሉም። እንዲያውም ኚአገራ቞ው ሰው ይልቅ ዹፈሹንጁን ምክር ዹበለጠ ዚሚያዳምጡና በሱ ዚሚመሩ ነው ዚሚመስለው። ይህ ዐይነቱ አካሄዳ቞ው በብሄራዊ ነፃነታቜንና በአገር ግንባታ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚኖሚው መገንዘብ ይቻላል። በውስጣ቞ውም ሰፊ ውይይት እንደማይካሄድ መናገር ይቻላል። ስለዚህም እንመራዋለን ዚሚሉትን ህዝብ በምን ፍልስፍና ላይ ተመስርተው እንደሚመሩትና፣ ለምን ዐይነቷ ኢትዮጵያ እንደሚታገሉና ምንስ ዐይነት ህብሚተሰብ መገንባት እንዳለበ቞ው ሲጠቁሙን አይታይም።

ወደ ጠቅላላው ህብሚተሰብአቜን ስንመጣ ደግሞ ሰፋ ያለ ዚሲቪክ ማህበሚሰብ እንቅስቃሎም ሆነ ባህል ዚለም። በተለያዩ መስኮቜ ህዝባቜን ሲጠቃ ይህንን ዹሚኹላኹልና ተግባራዊ እንዳይሆን በኹፍተኛ ደሹጃ እንቅስቃሎ ዚሚያደርግ ዚለም። ኚአንዳንዱ በስተቀር ምሁር ነኝ ዹሚለው አያገባኝም በማለት ህዝባቜንን ለብዙ አስ቞ጋሪና አደገኛ ነገሮቜ አጋልጩ እጁን አጣጥፎ ዹተቀመጠ ነው ዚሚመስለው። ለባህላቜን መኚስኚስ ተኚላካይ ዹሆነ ዚሲቪክ ማህበሚሰብ እንቅስቃሎ ዚለም። ህዝቡ መሬቱ ሲነጠቅ እሱን ለማገድ ዹሚደሹግ እንቅስቃሎ ዚለም። በኹተማው ውስጥ ህዝቡ ካለአግባብ ኚመሬቱና ኚቀቱ በልማት ስም ሲፈናቀልና፣ ለህብሚተሰቡ ዹማይጠቅሙ ህንፃዎቜ ሲሰሩ እሱን ለመኹላኹል ዹሚደሹግ ትግል ዚለም። ዹተበላሾ ዹአርኹቮክቾር አሰራር ሲስፋፋና ጌቶ ዚሚመስሉ ግንቊቜ እዚህና እዚያ  ሲገነቡ በሰው፣ በተለይም ደግሞ በታዳጊው ትውልድ ላይ ሊኖራቜው ዚሚቜለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ዹሚቃወምና ዚሚያጋልጥ ዚለም። በአሜሪካ ዹጂን ላቊራቶሪ ዚተዳቀለ ስንዎና በቆሎ ዚአገራቜን ገበሬ ሰለባ ሲሆን ይህንን ዚሚያጋልጥ ዚለም። ዚፖለቲካ ፓርቲዎቜም ዹዚህን አደገኛነት ዚተገነዘቡ አይመስልም። ኹዚህ ባሻገር ዚሙያ ድርጅቶቜ፣ ዚገበሬ ማህበራትና ዚሎቶቜና ዚወጣቶቜ ድርጅቶቜ ዚሉም። ባጭሩ ህብሚተሰብአቜን ቜግሩንና ብሶቱን ዚሚያሰማበትና ዚሚወያይበት እንዲሁም በጋራ ዚሚጋፈጥበት መድሚክ ዚለውም።

ወደ መንግስት መኪና ስንመጣ በብዙዎቻቜን ዘንድ ፊዩዳላዊ ዹሆነ አመለካኚት ነው ያለው። ለምሳሌ ዚአውሮፓን ዚህብሚተሰብ ታሪክና ዚመንግስት አወቃቀር ስንመለክትና፣ በዚህም ዙሪያ ዹተደሹገውን ዚመንግስት ቲዎሪ ስናነብ ዹምንገነዘበው በዹጊዜው ብቅ ያሉት ምሁራን ዚመንግስት አወቃቀርን ምንነትና፣ መንግስት በህብሚተሰቡ ውስጥ ዹሚኖሹውን ሚና በዚኀፖኩ ክርክርና ጥናት ሲያደርጉ ነበር። ኚእነ ፕላቶ ጀምሮ ኚክርስቶስ ልደት ኚስድስተኛው ክፍለ-ዘመን በኋላ ብቅ ያሉት ቀሳውስትና ፈላስፋዎቜ ስለመንግስት ምንነትና ሚና ያደርጉ ዹነበሹውን ክርክራና ጥናት መመልኚት ይቻላል። ዹሁሉም አቋም ታይራኖቜን ወይም አምባገነኖቜን አጥብቆ ዹሚቃውምና ዚህዝብን ማዕኹለኛ ቊታ ያስቀመጠ ኹፍተኛ መንግስታዊ አመለካኚት ነው። በሌላ አነጋገር፣ አንድ መንግስት ዚህዝቡን ደስታ ዚሚያሰቀድምና፣ ለዚህም ዚሚታጋል ታሪክ አሰሪ መድሚክ መሆን እንዳለበት ግንዛቀ ውስጥ ዚተገባና እንደመሰሚታዊ ቅድመ-ሁኔታም ዹተወሰደ ነው። በ17ኛውና በ18ኛው ክፍለ-ዘመን በጥበባዊ መንግስት ምስሚታ አስፈላጊነት ዙሪያ ዚተካሄደውን ጥናት መመልኚት ይቻላል። ዚእነሺለርና ሀርደር ዚጥበባዊ መንግስት ፍልስፍና ህዝብን በማዕኹላዊ ቊታ ያስቀመጠ ብቻ ሳይሆን፣ መንግስትና ህዝብ፣ መንግስትና ህብሚተሰብ ተለያይተው መታዚት ዚሌለባ቞ውና፣ መንግስትም ዚብልጜግናውን መንገድ ቀያሜ እንደሆነ ነው ዚሚያስተምሩን። ይህም ማለት በአውሮፓ ውስጥ ዚመንግስት አወቃቀር በጥናት ላይ ዹተመሰሹተ ብቻ ሳይሆን ኚታቜ ወደላይ ኊርጋኒካሊ እዚዳበሚና እያደገ ዚመጣ ሲሆን፣ በሌላ ወገን ደግሞ በካፒታሊዝም ውስጠ-ኃይል(dynamism) ጥገናዊ ለውጥን እዚተላበሰ ዚመጣ ነው። ማለትም ለካፒታሊዝም አጠቃላይ ዚሀብት ክምቜትና ስርዓቱ ካለብዙ መወዛገብ እንዲሰራ ተብሎ ዹተዘጋጀ ነው። ይሁንና በፓርቲዎቜና በመንግስት መኪና መሀኹል ግልጜ ልይነት አለ። ዚመንግስት መኪና በአንድ ፓርቲ ስር ዹወደቀና ወደ አገር አፍራሜነት ዹተቀዹሹ አይደለም። በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ በሎቢይስቶቜ ቁጥጥር ስር ያለ ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደሹጃ ደግሞ በአሞባሪነት ስም ጊርነትን ዚሚያካሂድና ደካማ አገሮቜን ዚሚያተራምስ ነው። በተለይም ዚሚሊታሪውና ዚስለላ ድርጅቶቶቜ በራሳ቞ው ዚሚንቀሳቀሱና ኚፓርሊያሚንት ቁጥጥር ውጭ ዹሆኑ ና቞ው።

ለማንኛውም ኢትዮጵያ ውስጥ አንዳቜ ዐይነት መሰሚታዊ ለውጥ ይምጣ ኚተባለ አሁን ባለው ዚመንግስት አወቃቀር ወደፊት መንቀሳቀስ አይቻልም። ብዙ ዚሶስተኛው ዓለም አገሮቜ ያሉት ቜግሮቜ በሙሉ እኛም አገር ውስጥ አሉ። ዚመንግስቱ መኪና በውጭ ዚስለላ ኃይል ዹተተበተበና ለህልውናቜንና ለብሄራዊ ነፃነታቜን ተቀናቃኝ ነው። በመንግስትና በህዝቡ እንዲሁም በጠቅላላው ዚህብሚተሰብ ክፍል መሀኹል ያለው መተሳሰብና መደጋገፍ በግልጜ ዚተቀመጡና፣ በዹጊዜው እዚተጠኑ ዚሚሻሻሉ አይደሉም። ዚኢትዮጵያን ህዝብ ጥቅምና ብሄራዊ ነፃነትን ዚሚያስኚብር መንግስታዊ አደሚጃጀትና አወቃቀር አይደለም በአገራቜን ምድር ያለው። አሰራሩና አወቃቀሩ ወደ ኋላ ዹቀሹ ነው። በዚሚንስትሪዎቜ ውስጥ ዚተቀመጡት ባለስልጣናት በውጭ ኃይሎቜና አማካሪዎቜ ዹሚጠመዘዙ እንጂ ለአገራቜን ዕድገትና ህልውና ዹቆሙ አይደሉም። ይህ ሁኔታ በአለፉት ሃያ ሰባት ዐመታት እዚተበላሜ ዚመጣና፣ ዚመንግስቱ መኪና ዚተለያዩ ዹውጭ ኃይሎቜ መፎካኚሪያ መድሚክ ሆኗል ማለት ይቻላል። በአገራቜን ዚሚታዚው ዚሃይማኖት፣ ዚብሄሚ-ሰብ ውዝግብና፣ በአማርኛ ቋንቋቜን ላይ ዹተደሹገው ዘመቻ ዚግዎታ ኹውጭ ኃይሎቜ ዚተንኮል ሞሚባ ጋር ዚተያያዘ ነው። ህብሚተሰብን በመበወዝ፣ በማኚሚባበትና ወደ ብጥብጥ እንዲያመራ በማድሚግ ዚተካነቜው እንግሊዝ ተቀዳሚውን ቊታ በመያዝ ህብሚተስብአቜን ወደ እርስ በርስ ጊርነት እንዲያመራ ዚማታደርገው ነገር ዚለም። አሜሪካም ኹዚህ ያላነስ ርኩስ ጚዋታ እንደሚጫወት ግልጜ ነው። ሌሎቜ ዚምዕራብ አውሮፓ መንግስታትም በእንደዚህ ዐይነቱ ያለመሚጋጋትና ዚተንኮል ስራ ዚሚጫወቱት ሚና ብዙ ዚሚጻፍለት ነው። ለምንድነው አነዚህ ዚአውሮፓና ዚአሜሪካ መንግስታት ይህን ዐይነቱን ተንኮል ዚሚሞሚቡት?  ነገሩን ለመሚዳት ብዙም መጹነቅ አያስፈልግም። እነዚህ ኃይሎቜ ወደዚህ ርኩስ ስራ ተሰማርተው ህዝብ እንዲበጣበጥ ዚሚሞርቡት ተንኮል አንድ ህዝብ በውዝግብ ዓለም ውስጥ ኹኖሹና ወደ ጊርነት ካመራ መስራትና ማድሚግ ያለበትን ታሪካዊ ድርጊት እንዳያኚናውን ይቆጠባል። ጭንቅላቱ በማይሆኑ ነገሮቜ ስለሚጠመድ ለማሰብና ለመፍጠር፣ እንዲያም ሲል አገር ለመገንባት ጊዜ ለማግኘት በፍጹም አይቜልም። ስለሆነም በታሪክ እንደታዚው ታታሪ አመራር ስልጣን ላይ ካለ እሱን ቶሎ ብለው ለማጥፋት ይጣደፋሉፀ ካለያም ደግሞ እንደዛሬው ሁኔታው ሲያመቻ቞ው በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ ሰርጎ በመግባት ብጥብጥ እንዲነሳ ያደርጋሉ። ይሁንና ዹውጭ ኃይሎቜ በአገራቜን ህልውና ውስጥ ገብቶ መፈትፈትና ወደብጥብጥ እንዲያመራ ማድሚግ በፓርቲ ደሹጃ ተደራጀን በሚሉት ዘንድ ግንዛቀ ውስጥ ዚተገባ አይመስልም። እንዲያውም አብዛኛዎቹ እነሱን አምላኪ በመሆን ብሶታ቞ውን ለማሰማት ሲሯሯጡ ይታያል። አብዛኛዎቹ ፓርቲዎቜም ሆነ ዚታወቁ ግለሰቊቜ ካለአሜሪካ ቡራኬና ፈቃድ ምንም ነገር ማድሚግ እንደማይቻል ነው ዚሚያወሩልን። አሜሪካ ዹሁሉ ነገር አድራጊና ፈጣሪ ተደርጎ ነው ዹሚተሹክልንና አምነንም እንድንቀበል ዚሚደሚገው። እነዚህ ድርጅቶቜም ሆነ አንዳንድ ግለሰቊቜ ያልገባ቞ው ነገር ሁሉም ነገር ኃላፊ መሆኑን ነው። ዛሬ ኃያል ዹሆነው መንስግስት ነገ በሌላ እንደሚተካ በፍጹም አልገባ቞ውም። ኹዚህ በተለዹ ግን ዚአሜሪካንን ዚበላይነት አምነው ሲቀበሉና ካለሱ ፈቃድ ምንም ነገር መስራት አይቻልም ብለው ሲሰብኩ እራሳ቞ው ሰው መሆናቾውን ይዘነጋሉ። ሁሉም ሰው በአምላክ ምስል ነው ዹተፈጠሹው ዹሚለውን ዚመጜሀፍ ቅዱስ አባባል ይስቱታል። ፈልግ ታገኛለህፀ ጠይቅ መልስም ታገኛለህፀ አንኳኳ በሩ ይኚፈትልሃልፀ እንድታይ ዐይን ሰጥቌአለሁፀ ዚምትመራመርበትንና ዚምትፈጥርበትም ጭንቅላት አለህ ዹሚለውን ግሩም ምሁራዊ አባባል ዹዘነጉ ይመስላሉ። ይህ ብቻ ሳይሆን በዚህ ዐይነት አስተሳሰባ቞ው ዚአገራ቞ውን ታሪክና እናቶቻቜንና አባቶቻቜን ብሄራዊ ነፃነታቜንን ለማስኚበር ያደሚጉትን ትግልና ዚኚፈሉትን መስዋዕትነት ይዘነጋሉ።

ኹዚህ ዚተወሳሰበው ሁኔታ ስንነሳ ዚፖለቲካው አደሚጃጀት ግልጜና በአንዳቜ ፍልስፍና ላይ ዹተመሰሹተ መሆን አለበት። ወደ ኹፍተኛ ምሁራዊ ውይይትና ክርክር ማምራት አለበት። ዚፖለቲካው መድሚክ ለማንም ተደራጀሁ ለሚል ሁሉ ክፍት መሆን ዚለበትም። ተደራጀሁ ዹሚል በሙሉ ፍልስፍናውንና ተግባራዊ ለማድሚግ ዹሚፈልገውን ፖሊሲ በግልጜ ወደ ወጭ አውጥቶ ለክርክርና ለውይይት ማቅሚብ አለበት። ማስሚዳትና ማስተማር አለበት። በሌላ ወገን ግን ዚአገራቜን ዚተወሳሰበ ቜግር በአንድ ድርጅት ወይም ፓርቲ ትኚሻ ላይ ብቻ ዚሚወድቅ አይደለም። ኚስልጣን ሜኩቻና እሜቅድምድሞሜ ባሻገር ሁሉም ኃይሎቜ ኚአዲስ አበባ እስኚሌሎቜ ክፍላተ-ሀገራት ወይም ክልሎቜ ድሚስ ዚሚካፈሉበት ሁኔታ መፈጠር አለበት። ስለሆነም በአገራቜንም ምድር በክልል ደሹጃ ተዘሹጋ ዚተባለው ፌዎራላዊ አስተዳደር ዚሚባለው ፈርሶ ተግባራዊ በሚሆን በክፍለ-ሀገራት ደሹጃ ቢዋቀር ሀብትን ለማንቀሳቀስና አገርን ለመገንባት ይቀላል። አብዛኛዎቹ በብሄር ደሹጃ ዚተዋቀሩ ክልሎቜ ክልሎቻ቞ውን ለማሰተዳደርና አዲስ ሀብት ለመፍጠር ቜሎታ ስለሌላ቞ው አዲስ ዚፖለቲካ ባህል መዳበርና አዳዲስ ኢንስቲቱሜኖቜ መቋቋም አስፈላጊና ወሳኝ ና቞ው። ሰፋ ባለና በሁሉም አኳያ በሚገለጜ በኹፍተኛ ዕውቀት በተካነ ኢንስቲቱሜናዊ አወቃቀር ብቻ ነው አንድን አገር መገንባት ዚሚቻለው። ዹሰውን ኃይልና ዚተፈጥሮን ሀብት ማንቀሳቀስና ለአገር ግንባታ አውሎ ህዝቡ እንዲጠቀመው ለማድሚግ ዚግዎታ ዹሰለጠነ ዹሰው ኃይል ያስፈልጋል። ታታሪና ማሰብ ዚሚቜል ኃይል እዚተኮተኮተ ቊታ መያዝ አለበት። በዚህ አማካይነት ብቻ ነው ዛሬ ዚተስፋፋውን ሙስናዊ አስተዳደርና ዚሀብት መባኚንን፣ እንዲሁም ዹውጭ ኢንቬስተር ነን ባዮቜን ዘሹፋና አገር አጥፊነት መቋቋም ዚሚቻለው።

ለዚህ ቁልፉ ደግሞ ዲሞክራሲያዊ ነፃነት ኚአላንዳቜ ገደብ መስፈን አለበት። ዲሞክራሲ ሲባል እንዲያው በዚአራት ዐመቱ ምርጫ እዚተካሄደና ወካይ ነን ባዮቜን እያዩ መኖር ሳይሆን በእርግጥም ህዝቡ ደሹጃ በደሹጃ ራሱ ዚሚደራጅበትንና ሃሳቡን እዚገለጞ በአገር ግንባታ ውስጥ ዚሚሳተፍበት ሁኔታ መፈጠር አለበት። ዚመሳተፍና ዚሃሳብ ገለጻ ብቻ ሳይሆን እንደዚህ ዐይነቱ ዲሞክራሲ ተወካይ ነን ዚሚሉትንም ዚመቆጣጠሪያ መሳሪያ መሆን አለበት። እንደ ኢትዮጵያ ባለ በብዙ ሺህ ቜግሮቜ በተተበተበት አገርና፣ ድህነትና ዚኑሮ ምስቅልቅልነት አፍጩ አግጩ በሚታይበት አገር ቜግሩን በተወካዮቜ ብቻ መቅሹፍ አይቻልም። ዲሞክራሲን ተግባራዊ ለማድሚግ ደግሞ ዚግዎታ ህዝቡ እንዲማርና እንዲያውቅ፣ እንዲሁም ጥያቄዎቜን እንዲጠይቅ ስፋ ያለ ዚትምህርት ተቋማት መዘርጋት አለበት። በተለይም ተራው ህዝብ ኚስራ በኋላ ማታ ማታ እዚሄደ አዲስ ዕውቀት ዚሚቀስምበት ህዝባዊ ባህርይ ያላ቞ው ዚሙያና ዹቀለም እንዲሁም ልዩ ልዩ ስልጠናዎቜን ዚሚሰጡ ዚህዝብ ትምህርትቀቶቜ መቋቋም አለባ቞ው። በተጚማሪም በቀላል ቋንቋ ዚማማሪያ መጜሀፎቜን እያዘጋጁ ማደል ያስፈልጋል። እንደሚታወቀው ለአንድ አገር ዕድገትና ተቻቜሎ መኖር ዚግዎታ ዕውቀት መሰሚታዊ ቊታን ይይዛል። ዕውቀት ባልተስፋፋበት፣ ጥቂት ተማርን ዹሚሉ ስልጣን በጚበጡበትና ዹፈለጋቾውን ፖሊሲ እያወጡ ተግባራዊ በሚያደርጉብት አገር ዚመጚሚሻ መጚራሻ አለመሚጋጋትና ድህነት ይፈጠራሉ። ዕውነተኛ ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር ባልሰፈነባ቞ውና ዕውቀት ባልተስፋፋባ቞ው አገሮቜ ዹምንመለኹተው ሀቅ መመሰቃቀልንና ብጥብጣን፣ ዚመጚሚሻ መጚሚሻም መሰደድን ነው። ስለዚህም ዚህዝቡ ተሳትፎ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለዲሞክራሲያዊ አገር ግንባታ ወሳኝ ሚናን ይጫወታል።

ኹዚህ ስንነሳ ዚፖለቲካን ምንነት ወይም ተግባር በመጠኑም ቢሆን ግንዛቀ ውስጥ ማስገባት ያስፈልጋል። በመሰሚቱ ፖለቲካ ዚአንድን አገር ህዝብ ማስተዳደሪያ መሳሪያ ነው። ፖለቲካ አንድን አገር ጥበባዊ በሆነ መልክ ለማስተዳደር፣ በህብሚተሰብ ውስጥ ያሉና ሊኚሰቱ ዚሚቜሉ ቅራኔዎቜ እንደዚሁኔታው ሊፈቱ ዚሚቜሉበትን ዘዮ መፈለጊያ መሳሪያ ነው። ፖለቲካ በመሰሚቱ ለጥቂቶቜ ዹተሰጠና ዚሚሰጥ፣ አንድን አገር እንደፈለጋ቞ው ሊበውዙበት ዚሚፈቀድላ቞ው መሳሪያ አይደለም። ፓለቲካ ዹአገር ማስተዳደሪያ ጥበብ እንደመሆኑ መጠን አንድ ህዝብ በትክክለኛ አመራር ታሪክን እንዲሰራ ማዘጋጃ መሳሪያ ነው። ይህ አስተሳሰብ ዚግዎታ ጭንቅላት ውስጥ መያዝ አለበት። በሌላ ወገን በአገራቜንም ሆነ በተቀሩት ዚአፍሪካ አገሮቜ ያለው ዚፖለቲካ እሰተሳሰብ ግንዛቀ ዚጥቂቶቜ ግል ሀብት ይመስል ህብሚተሰብን ማኚሚባበቻና ማዘበራሚቂያ መሳሪ ወደመሆን ተለውጧል። ለዚህ ዋናው ምክንያት በዚአገሮቜ ውስጥ ዚፖለቲካ ባህል አለመዳብር፣ ሰፋ ያለ ምሁራዊ እንቅስቃሎ አለመኖር፣ ኹዚህም በመነሳት ጥቂት ፖለቲኚኛ ነን ባዮቜ እንደ አምላክ ዚሚቆጠሩበትና ያሻ቞ውን ለማድሚግ ዹተፈቀደላቾው ይመስል ህገ-መንግስትና ህዝብ ሳይፈቅድ ኹሌላ መንግስት ወይም ኩባንያ ጋር ስምምነት በመፍጠር ዹአገርን ጥሬ ሀብት ዚሚ቞በቜቡበት፣ ዹጩር ካምፕ ዚሚሰጡበትና ዚስለላ መሚብ እንዲዘሚጋ በማድሚግ ነጻነት እንዳይኖር ዚሚያደርጉ ሁኔታዎቜ በብዙ ዚአፍሪካ አገሮቜና በእኛም አገር ተስፋፍተዋል። ይህ ዐይነቱ አመለካኚት እስካለና፣ አንዳንድ ግለሰቊቜ ተሰባስበው ፓርቲ ዚሚባል ነገር ኚመሰሚቱ በኋላ ቡራኬ ለማግኘት ሲሉ ወደ ትላልቅ ኀምባሲዎቜ ዘንድ ዚሚያመሩና ራሳ቞ውን ዚሚያስተዋውቁ ኹሆነ እንደነዚህ ዐይነት ሰዎቜ ኚመጀመሪያውኑ ዚፖለቲካ ትርጉም ምን እንደሆነ አልገባ቞ውም ማለት ነው። ዹውጭና ዚውስጥ ፖለቲካ ዚሚባል ነገር ቢኖርም፣ ለፖለቲካ ስልጣን እታገላለሁ፣ ህዝብ አስተዳድራለሁ፣ በዚያውም ታሪክ እንዲሰራ አደርጋለሁ ዹሚል በመጀመሪያውኑ መሚዳት ያለበት ለአገሩና ለህዝቡ ተገዢና ተጠሪ መሆኑን ነው። ይህ ግልጜ ሲሆን ብቻ በፓርቲ ደሹጃ መደራጀትና መወዳደር ይቻላል።

ያም ሆነ ይህ አገራቜንን በአዲስ ዚፖለቲካ አደሚጃጀት ለማዋቀርና፣ ዚፓርቲ ጜንሰ-ሃሳብ ትርጉም በጭንቅላት ውስጥ እንዲቀሚጜ ለማድሚግ ዚግዎታ ዚፖለቲካ ሬናሳንስ ያስፈልጋል። ሰፋ ያለ ውይይትና ክርክር ወሳኝ ና቞ው። ይህንን ሆነ ወይም ያኛውን ስም በመለጠፍ ድርጅት ነን ብለው በአዲስ አበባ ብቻ ተወስነው ዚሚንቀሳቀሱ እዚተነሱ ዚሚፈነጩበትና አገራቜንም ዹውጭ ኃይሎቜ መጚፈሪያ ዹመሆኑ ጊዜ ማብቃት አለበት። እንደፓኪስታንና እንደሌሎቜ ዚሶስተኛው ዓለም አገሮቜ ዚአስተዳደር ቜግር እንዳይፈጠር ኹተፈለገ በግልጜ ኚመወያዚት ሌላ አማራጭ ነገር ዚለም። ስለሆነም አዲስ ዹክርክርና ዚውይይት ባህል እንዲሁም ግልጜነት እጅግ አስፈላጊዎቜ ና቞ው። ይህንን ዐይነቱን ክርክርና ውይይት ላለመጋፈጥ ለመሞሞ ዹሚሞክር ካለ ዚራሱ ዹሆነ ዹተደበቀ ዓላማ አለው ማለት ነው።

ዚህብሚ-ብሄር ዚመንግስት (Nation-State) ጉዳይ!

እንደሌሎቜም ጉዳዮቜ ዚህብሚ-ብሄር ጉዳይ አስፈላጊነት ዚሚያኚራክርና ኢትዮጵያንም እንደ አገርና እንደ ህብሚተሰብ ያለመውሰድና አምኖ ያለመቀበል አዝማሚያ ይታያል። እንዲያውም አንዳንዶቹ ኢትዮጵያን ገነጣጥለው ዚዚራሳ቞ውን ትናንሜ መንግስታት ቢመሰርቱ ደስታውን አይቜሉትም። በእኛም ለህብሚ-ብሄርና ለአንድ ኢትዮጵያ እንታገላለን በምንለው ዘንድ ጜንሰ-ሃሳቡ በግልጜ ዹተቀመጠና እንድንወያይበት ዹተደሹገ አይደለም።

ዚህብሚ-ብሄር ምስሚታ ዚታሪክ ግዎታ ነው። በተለያዩ አገሮቜ ዚተለያዚ ሂደት ቢወስድምና፣ ህብሚ-ብሄሮቜ ቢመሰሚቱም በህብሚተሰብ ታሪክ ውስጥ በአውሮፓ ምድር ውስጥ ብቻ ነው ዹተጠናቀቀ ህብሚ-ብሄር ሊዋቀር ዚቻለው። ዚአውሮፓ አገሮቜ እንደ አንድ ወጥ መንግስት ኹመቋቋማቾው በፊት በአንድ አገር ውስጥ ትናንሜ መንግስታት እንደነበሩና ሰፋ ላለ ዚገበያ ኢኮኖሚና ለህብሚተሰብ አወቃቀር አስ቞ጋሪ ሁኔታ ተፈጥሮ እንደነበር ግልጜ ነው። ለምሳሌ ጀርመንን ብንወስድ እ.እ እስኚ 1871 ዓ.ም ድሚስ ወደ ሶስት መቶ ዹሚጠጉ ዚመሳፍንት አገዛዞቜ እንደነበሩ ይታወቃል። በዚህም ምክንያት ዚተነሳ ኚአንዱ ግዛት ወደ ሌላ ለመሄድ ዚጉምሩክ ቀሚጥ መክፈል ዚግዎታ ነበር። ጀርመንም እንደ አገርና እንደህብሚ-ብሄር ያልተዋቀሚቜ ስለነበሚቜ በተለያዩ ዹወጭ ወራሪዎቜ፣ በስዊድን፣ በዎንማርክ፣ በፈሚንሳይና በአውስትሪያ በተደጋጋሚ ስትጠቃ ነበር። በሌላ ወገን ግን ዚተለያዩት ዚመሳፍንት አገዛዝ በዚራሳ቞ው ክልል ውስጥ ትናንሜ ዹጎጆ ኢንዱስትሪዎቜና ሰፋ ብሎ ዹተዘሹጋ አስተዳደር ነበራ቞ው። በደንብ ዚተዋቀሩም ዹማዕኹለኛው ክፍለ-ዘመን ኚተማዎቜ ነበሯ቞ው። ዚስራ-ክፍፍልም ይታይ ነበር።  ይህ ሁኔታና በኋላ ላይ ዚፕሚሺያ አገዛዝ ተጠናክሮ መውጣትና፣ አልፎም አንዳንዶቜን በጩር ኃይል በቁጥጥር ስር ማዋል ለጀርመን አንድ ወጥ መንግስት በ1871 ዓ.ም መመስሚት መንገዱን አዘጋጀ። በዚህም ምክንያት ዚህብሚ-ብሄር መንግስት ዹሚለው አስተሳሰብ እንዲቀሚጜና ይህንን ሊያሰተሳስር ዚሚቜል ሰፋ ያለ በማኑፋክቱር ላይ ዹተመሰሹተ ዚኢንዱስትሪ አብዮት ማካሄድ አስፈላጊ ሆነ። ቀስ በቀስም ዚውስጥ ገበያ ሲዳብርና በአንድ ገንዘብ አማካይነት ዚንግድ ልውውጥ ሲዳብርና ዚባቡር ሃዲድ ሲዘሚጋ ዹኹበርቮው መደብ ዚበላይነቱን ተቀዳጀ። አገር፣ ህብሚ-ብሄርና ባንዲራ፣ እንዲህም ህዝብ ዹሚለው ጜንሰ-ሃሳብ ተቀባይነትን አገኙ። ስለሆነም ዹጀርመንም ሆነ ዚእንግሊዝ ወይም ዚፈሚንሳይ ህዝብ በዚአገሮቻ቞ው እንደ አንድ ህዝብ ዚሚቆጠሩ እንጂ፣ እንደ አገራቜን ዚኊሮሞ ህዝብ፣ ዚአማራና ዚትግሬ ወይም ዹሌላ ህዝብ እዚተባለ አይደለም ዚሚጠራው። ይህ ዐይነቱም አባባል ሳይንሳዊ አይደለም። ምክንያቱም አንድ ብሄር ወይም ብሄሚ-ሰብ እንደ አንድ ህዝብ ዚሚታወቀውና ዚሚጠራው ለአንድ ህብሚተሰብ መኖርና መንቀሳቀስ ዚሚያስቜሉትን፣ ፓለቲካዊ፣ ርዕዮተ-ዓለማዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ባህላዊና ስነ-ምግባራዊ፣ እንዲህም ዚራሱ ዹሆነ ዚመነጋገሪያ ቋንቋ ብቻ ሳይሆን ዚመጻፊያም ቋንቋና ሌሎቜ ሌሎቜ ነገሮቜን አሟልቶ ሲገኝ ብቻ እንደ አንድ ህዝብ ሊቆጠር ይቜላል። በተጚማሪም በስራ-ክፍፍል ዚዳበሚ ኹሆነና ዚራሱ ዹሆነ ቢሮክራሲያዊ አወቃቀር ካለው እንደ አንድ ህዝብ ሊቆጠር ይቜላል። ይሁንና ወደ ህብሚተሰብ ሳይንስ ወይም ሶስዮሎጂ ስንመጣ በአንድ አገር ውስጥ አንድ ህዝብ አለ ብሎ መናገር ቢቻልም ሁሉም አንድ ዐይነት ስነ-ልቩናዊና ያለውና በአንድ ዐይነት ሙያ ዹሰለጠነ አይደለም። በሌላ አነጋገር በገቢ ደሹጃ ወይም በመደብ ዹተኹፋፈለ ነው ማለት ነው። ይህ ደግሞ በራሱ ብሄሚሰብ ዹሚለውን ውስን አስተሳሰብ ዹሚቃሹን ነው። ስለሆነም በሳይንስ ስሌት ብሄሚሰብ ዹሚለው አባባል ቊታው አይኖሹውም ማለት ነው። አንድን ብሄሚሰብ ብሄሚሰብ ተብሎ ዚሚያስጠራው በራሱ ዚስራ-ክፍፍል ኹሌላና ኹሌላው ጋር ዹማይገናኝና ተዘግቶ ዹሚኖር ኹሆነ ብቻ ነው። እንደዚህ ዐይነቱን አደሚጃጀት ደግሞ በ21ኛው ክፍለ-ዘመን ፈልጎ ማግኘት ያስ቞ግራል። ግሎባል ካፒታሊዝም ሁሉንም አገሮቜ አመሰቃቅሎአ቞ዋል። ኹክልል ውጭ ወጥተው እንዲንቀሳቀሱ አስገድዷ቞ዋል። በሌላ ወገን ኚዕውቀት ማነስ ዚተነሳ ዚማንነት መለያ ዹሚለውን አንጠልጥለው በመዞር በቅዠት ዓለም ውስጥ እንዲኖሩ ተገደዋል።

ወደ ኢትዮጵያቜን ስንመጣ በአገራቜን ውስጥ ዚህብሚ-ብሄርን ጜንሰ-ሃሳብ ለማስሚገጥና፣ ብሄራዊ ተቀባይነት እንዲኖሚው ለማድሚግ ዹተፈጠሹው ቜግር በዚብሄሚ-ሰቡ ውስጥ ኚበር቎ያዊ አስተሳሰብ መዳብር ባለመቻሉ ነው። ለዚህ ደግሞ ዋናው ምክንያት ዚብዙዎቹ ብሄሚ-ሰብ ኢኮኖሚዎቜ አወቃቀር፣ በኚብት እርባታ፣ በግብርናና በዘላንነት ወይም በአዳኝነት ላይ ዹተመሰሹተ በመሆኑ ነው። በዚብሄሚ-ሰቡ ውስጥ በጎጆ ኢንዱስትሪ ላይ ዹተመሰሹተ ምርታዊ ክንውን ባለመኖሩና ዚስራ-ክፍፍሉም ዚዳበሚ ስላልነበር ዚውስጥ ገበያን ማዳበር አልተቻለም ነበር። በአስተዳደርም ደሹጃ ዹተዋቀሹ ቢሮክራሲያው ነክ አደሚጃጀት አልነበሚም። በዚህ መልክ ተዝሚክርኮ ዹተዋቀሹው ኢኮኖሚያዊ ክንዋኔ ለሌሎቜ ባህላዊ ዕድገቶቜና እንቅስቃሎዎቜ፣ ለምሳሌ ለሊትሬ቞ር፣ ለሙዚቃ፣ ለፍልስፍና ለአርኪ቎ክ቞ርና ለልዩ ልዩ ህብሚተሰቡን ሊያስተሳስሩ ለሚቜሉ ነገሮቜ መዳበር አመቺ አልነበሚም። ይሁንና ግን ዚኢትዮጵያን ዚንጉሳዊ ታሪክ ባህል ስንመለኚት ወደ ህብሚ-ብሄሚሰብም ዚማምራት አዝማሚያና ህዝቡን ሊያገናኘው ዚሚቜል ባህላዊ ምልክቶቜ ነበሩፀ አሉም።

ዚኢትዮጵያን ታሪክና ዚህብሚተሰብ አወቃቀር አስ቞ጋሪና በጥያቄ ውስጥ እንዲገባ ዚሚያደርገው ሌላው ጉዳይ፣ ዚህብሚ-ብሄር ምስሚታ ኚኢምፔሪያሊዝም አይሎ መውጣት ጋር መጋጚቱና፣ ወደ ውስጥ ያተኮሚ ሰፋ ያለ ዚኢኮኖሚ ግንባታ መዘርጋት ያለመቻሉ ነው። በ19ኛ ክፍለ-ዘመን አይሎ ዚወጣው ኢምፔሪያሊዝም እንደሌሎቜም ዚአፍሪካ አገሮቜ ዚኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ማጹናገፍ ጀመሚ። ለኢንዱስትሪ ምስሚታና ለውስጥ ገበያ መዳበር እንቅፋት ሆነ። እንደ ጃፓን ዹሚጄ ዲይናስቲ ዐይነት ቆራጥ አገዛዝ ባለመፈጠሩ ኢትዮጵያ ለኢምፔሪያሊዝም መጚፈሪያ መድሚክ ሆነቜ። ሃሳቡ ዚተጋጚበትና ዚሚጋጭበት፣ ዚማንነት ቀውስ ዹተዋሃደው ዚህብሚተሰብ ክፍል ብቅ አለ። በዚህም ምክንያት ኚዚብሄሚ-ሰቡ ዚወጣው ኀሊት ነኝ ባይ ብቻ ሳይሆን ራሱ ኢትዮጵያዊ ነኝ፣ በኢትዮጵያዊነ቎ እኮራለሁ ዹሚለው ዹአገር-ወዳድነት ስሜት ቜግር ተፈጠሚበት። ይህንን በሚገባ ለመሚዳት ዘርዘር አድርጎ መመልኚት ያስፈልጋል።

ኹሁለተኛው ዓለም ጊርነት በኋላ ዹተፈጠሹው ሁኔታ ዚባሰውን ዚኢትዮጵያን ኢኮኖሚ አዘበራሚቀው። ግልጜ ዚውስጥ ገበያ ማዳበር አለተቻልም። ኚበርቲያዊ መደብም መፍጠር አልተቻለም። በዚህም ምክንያት ዚተነሳ ዹተዝሹኹሹኹው ኢኮኖሚ ብሄራዊ ንቃተ-ህሊናን ሊያዳብር ዚሚያስቜልና እንደ አንድ ህዝብ እንድንነሳ ዚሚያደርገን አልነበሚም። በተለይም በ1950ኛው ዓመተ ምህሚት መጀመሪያና ኚዚያ በኋላ ተግባራዊ መደሹግ ዚነበሚበት ሰፋ ያለ ዚኢኮኖሚ ተቋምን ማዋቀርና ህብሚተሰቡን ማያያዝ፣ ብሄራዊ ባህይርና ብሄርተኝነት እንዲፈጠር ኚአዲስ አበባ ውጭ ባህላዊ እንቅስቃሎዎቜን፣ ለምሳሌ እንደ ቲያትር ቢቶቜና ሌሎቜንም ማስፋፋትና ማዳበር ሲገባ፣ አገዛዙ ሆን ብሎ ዚያዘው አትኩሮውን በአዲስ አበባ ብቻ መወሰን ነበር። ፍሪድርሜ ሺለር እንደሚለን አንድ አገር እንደ ህብሚ-ብሄር እንድትዋቀርና እንድትገነባ ኹተፈለገ ኚኢኮኖሚና ኚኚተማዎቜ ግንባታ ባሻገር ብሄራዊ ባህርይ ያለው ዚድራማና ዚቲአትር መድሚክ በአገር ውስጥ ማስፋፋት ያስፈልጋል ይላል። ይህ ዐይነቱ አስፈላጊ ጉዳይ ተግባራዊ ሊሆን ባለመቻሉ ዚግዎታ ዚፊዩዳላዊ ዚማፍንገጥና ዚማኩሚፍ ሁኔታ መፈጠሩ አይቀርም። ስለሆነም መጠናቀቅ ያለባ቞ው ህብሚ-ብሄራዊ ዚግንባታ መሰሹተ-ሃሳቊቜ ለአፈንጋጭ ኃይሎቜ ሁኔታውን አመቻቜቶ ሰጣ቞ው። ዹዚህም ሆነ á‹šá‹šá‹« ተጠሪ ነን፣ ለነፃነት እንታገላለን ዹሚሉ በእርግጥ ደግሞ ዚነፃነትን ትርጉም ያልተገነዘቡ ዚብሄሚ-ሰብ አንቅስቃሎዎቜ ብቅ አሉ። በሰላምና በውይይት፣ እንዲሁም በክርክርና በኹፍተኛ ንቃተ-ህሊና ለአንድ ዓላማ ለመታገል ሰፊ መድሚክ እንዳይፈጠር መንገዱን ዘጉ። ይህ ዐይነቱ ሁኔታ አርቆ-አሳቢነት ወደጎደለው ወደ እርስ በርስ ጊርነት ሲያማራን፣ በዚያው መጠንም ኃይልን አስተባብሮ አንድ ዲሞክራሲያዊና ሪፑብሊካዊ እንዲሁም ጠንካራ አገር እንዳንመሰርት አገደን። ኹፍተኛ ዹሆነ ዹሰውና ዚማ቎ሪያል እንዲሁም ዚገንዘብ ኃይል ወደመ። ለዚህ ዐይነቱ ዚህብሚ-ብሄር ግንባታ ዕንቅፋትም ሌላው ምክንያት ራሱ አገዛዙ በኀምፔሪያሊዝም ጉያ ስር መውደቁ ነው። ወታደሩ፣ ዚስለላ መዋቅሩና ፖሊሱ ሁሉ በውጭ ኃይሎቜ ዚተገነቡ ስለነበር ኚውስጥ ሆኖ ለማመስ ቀላል ነበር። ዚሲቪል ቢሮክራሲውም አስተሳሰብ ብሄራዊ ንቃተ-ህሊና ዹጎደለው ስለነበር ለአገር ግንባታ አስተዋፅዖ ሊያደርግ አልቻለም። እንዲያውም እንቅፋት በመሆን ኚውስጥ ብሄራዊ ነፃነታቜን እንዲቊሚቊር አደሚገ።

ባለፉት ሃያ ሰባት ዐመታት ዹተዋቀሹው ዹክልል አገዛዝ ሁኔታውን አባባሰው። ዚህዝቡን አመለካኚት አዘበራሚቀው። ኢኮኖሚውን በዘሹፋ ላይ እንዲካሄድ አደሚገው። ኚተማዎቜ ወደመንደርነት እንዲለወጡ አደሚገ። ባጭሩ ለጠንካራ አገር መገንባት መሰናክሎቜ ፈጠሚ። በዚህ ዐይነት ዹተዝሹኹሹኹ ህብሚተሰብና ዚኢኮኖሚ አወቃቀር እንዎት ተደርጎ አገርን መገንባት ይቻላል? እንዎትስ ብሄራዊ ስሜትን ማዳብር ይቻላል? በሚለው ላይ በሰፊውና ብግልጜ መነጋገር ዚሚያስፈልግ ይመስለኛል። ዹውጭ ኃይሎቜንም አሻጥር በግልጜ መነጋገርና ድርጊታ቞ውንም ገደብ እንዲኖሚው  ማድሚግ ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ ዚእኛ ንቃተ-ህሊንና ዹምሁር ኃያልነት እጅግ አስፈላጊ ነው። ለዚህ ደግሞ ዚእኛ በአንድነትና ለአንድ ዓላማ መቆማቜን ወሳኝ ነው። ለማንም ዹውጭ ኃይል ቀዳዳ ዚማንሰጥና ዕውነተኛ ብሄሚተኝነት ዚተላበስን መሆን አለብን። በተጚማሪም በሁሉም መልክ ዚሚገለጜ ምሁራዊ ኃይልና ኃያልነት መኖር አስፈላጊ ነው። አገራቜን ዚኢምፔሪያሊስቶቜ፣ በተለይም ዚአሜሪካን ኢምፐሪያሊዝም መጚፈሪያ እንዳትሆን በትጋት መስራት ያስፈልጋል። ዚሚያሳዝነው ነገር ለዚህ ዐይነቱ ግልጜ ውይይት ተቃዋሚ ነኝ ዹሚለው ኃይል ዝግጁ አለመሆኑ ነው። እንዲያውም አንዳንዱ ዕድሉንና ዚስልጣን መያዙን ጉዳይ ኚአሜሪካን ጋር ያገናኘ ነው ዚሚመስለው። በዚህም በዚያም ብሎ ይህ ነገር እንዲነሳበት አይፈልግም። ድሮም ሆነ ዛሬ በደፈናው ለብሄሚ-ሰቀ ነፃነት እንታገላለን ዹሚለውን ብቻ ፀሹ-ኢትዮጵያና ዚአንድነት ፀር አድርጎ መወሰድ አይቻልምፀ ትክክልም አይደለም። ለዛሬይቱ ኢትዮጵያ በዚህ ዐይነት ሁኔታ ውስጥ መገኘት በብሄር አቀፍ ደሹጃ ተደራጀሁም ዹሚለው ተጠያቂ ነው። ድሮም ሆነ ዛሬም አቋሙ ግልጜ አይደለም። በእዚአንዳንዱ ነጥብ ላይ ግልጜ አቋም ኹሌለንና ለማስሚዳት ካልቻልን፣ ኹዚህም ባሻገር ዚውስጥ ለውስጥ አሻጥር ዚምንሰራና መሰናክል ዚምንፈጥር ኹሆነ እንዎት አድርገን ነው ለብሄራዊ አንድነት መታገል ዚምንቜለው። በአንዳንዶቻ቞ን ዘንድ አሁንም ቢሆን ዚድሮው ዚተማሪው ዐይነት እንቅስቃሎ ሁኔታ ነው እንጂ ዚሚታዚው ኚበር቎ያዊና ምሁራዊ አስተሳሰብ ማዳበር በፍጹም አልቻልንም። ቶሎ ብለን ወደኩርፊያና ወደ መሻኮት እናመራለን። ቡድናዊ ስሜት እናዳብራለን። በሃሳብና በምሁራዊ ውይይት ዙሪያ ሰውን ለመሰብሰብ ኹመሞኹር ይልቅ አግበስብሰን ተኚታዮቜን ለማፍራት እንሜቀዳደማለን። ስለሆነም ኹዚህ ዐይነቱ ዚመሜሎክለክ ጚዋታና ሜወዳ እስካልተላቀቅን ድሚስ አስር ጊዜ ኢትዮጵዊ ነን፣ ኢትዮጵያቜንም ዘለዓለም ትኑር እያልን ብንጮህ ትግሉን ኹማጹናገፍ በስተቀር ሌላ ዚምንሰራው ቁም ነገር ዚለም።

ለብሄሚሰብ ነፃነታቜን እንታገላለን ዚምትሉ ደግሞ በጠቅላላቅው ያለንን ደካማና አስ቞ጋሪ ሁኔታ በመገንዘብ ሰፋ ላለ ምሁራዊ ውይይት መዘጋጀት አለባቜሁ። ኹመገንጠል ሌላ አመራጭ ዚለንም፣ ብሄሚ-መንግስት ነበሚን፣ እሱን መልሰን መቀዳጀት አለብን እያላቜሁ ወደማይደሚስ ህልም ዹሚደሹገው ምሁራዊነት ዹጎደለው ትግል ዚመጚሚሻ መጚሚሻ ሁላቜንንም ያጠፋናል። እያንዳንዱ ግለሰብ ምኞቱን ተግባራዊ ማድሚግ ዚሚቜለውና ዹሚመኘውን ማግኘት ዹሚቾለው በኢትዮጵያ ውስጥ ነው። ምን ዐይነት ፊዎራላዊ አወቃቀርና ዚሪፑብሊክ አመሰራሚት ነው ዚሚያዋጣው በሚለው ላይ  መነጋገር ያስፈልጋል። በሌላ ወገን ግን በቁጥር ዚምንበልጥ አኛ ነን፣ ስልጣን ዚሚገባን ለኛ ነው ዹሚለው አነጋገርና መመጻደቅ አደገኛ አካሄድ ነው። በቁጥር በልጩ መገኘት ሳይሆን ዋናው ቁም ነገር ጥራት ያለው ግልጜ ዹሆነ ምሁራዊና ሳይንሳዊ ትግል ነው ወሳኝነት ዚሚኖሚው። ቜግሮቜ እንዎት እንደሚፈቱ በሳይንሱ ማሳዚት ነው። ያም ሆነ ይህ ዚዛሬይቱን ኢትዮጵያ መኹፋፋል አይቻልም። ወያኔም ባለፉት ሃያ ሰባት ዐመታት ሞክሮ ሞክሮ አልተሳካለትም። ጠቅላላው ዚኢትዮጵያ ህዝብ ምኞቱንና ፍላጎቱን አንድ ላይ ብቻ ሆኖ ዕውን እንደሚያደርግ ኹምንጊዜውም በላይ ተገንዝቧል። ይህንን ዚህዝብ ፍላጎትና ስሜት መቀበል ያስፈልጋል። ኢትዮጵያውነቱን እንዲሜር መግትጎትና በብሄሚ-ሰቡ ብቻ ዕምነት እንዲኖሚውና እንደርዕዮተ-ዓለም እንዲቀበለው ዹሚደሹገው አጉል ቅስቀሳ ዚታሪክ ወንጀል መስራት ነው። ወደ ጭፍንነትና ወደ እርስበርስ ጊርነት ዚሚያመራ ነው። ዹሰውን ልጅ ታሪካዊ ተልዕኮ ዹሚፃሹር ነው። ስለዚህም ግለሰብአዊ ነፃነትና በብሄር ግንባር ዹማይወኹል ህዝባዊ መብት ዚሚኚበርበትን አገር ዚመፍጠሩ ጉዳይ ወሳኝ ይሆናሉ። ለዚህ ደግሞ ዋናው ቁልፍ ጉዳይ ድህነትንና ሚሃብን አስወግዶ ጠንካራ ዹሆነ ብሄሚ-አቀፍ ኢኮኖሚ መገንባት ነው። በብሄሚ-ሰብ ደሹጃ ተደራጀን ዹሚሉ በመሰሚቱ ዚዚብሄሚ-ሰቊቻ቞ውንና ዚግለሰቊቜን መብት ማስጠብቅና ማስኚበር አይቜሉም። በታሪክ እንደታዚው ተጠቃሚው ኀሊቱ እንጂ ሰፊው ብሄሚ-ሰብ አይደለም። ይህ ዐይነቱ አስተሳሰብና አካሄድ ለንዑስ ኹበርቮው ፋሺሜታዊ መሰሚት ይጥልለታል። ኹግላዊ ነፃነትና አገራዊ ብልጜግና ይልቅ ድህነትና ድንቁርና ይስፋፋሉ። ይህ በራሱ አገርን ለውጭ ጠላት አጋፍጩ ያሰጣል። ዚተዳኚመና ዚተበታተነ አስተሳሰብ ያለው ህዝብ ለውጭ ወራሪዎቜ አመቺ ነው።፡

ሌላው በግንዛቀ ውስጥ መግባት ያለበት ጉዳይ ልዩ ልዩ ነገሮቜና አንድነት ተያይዘው ዚሚሄዱና ዚተፈጥሮ ህግም ና቞ው። እንደሚታወቀው ዹሁሉም ነገር ምንጭ አንድ ነገር ብቻ ነው። ኚዚያ አንድ ነገር በመነሳት ነው ሌሎቜ ነገሮቜ እዚተለያዩና እዚተሰበጣጠሩ ዚመጡትና ዚሚመጡት። ይሁንና ግን እነዚህ ዚተለያዩ ነገሮቜ(diversified) እዚያው በዚያው በአንድነት ዚሚኖሩ እንጂ እንደጠላት ተለያይተው ዚሚኖሩ አይደሉም። ተፈጥሮ በተለያዩ አፅዋዕትና እንስሳት ሁሉ ዚምትገለጜ እንደመሆኗ መጠን፣ በዚህም አማካይነት ብቻ ዚተለያዩ አፅዋዕትና እንስሳት በተፈጥሮ ውስጥ ዚሚደርስባ቞ውን ጥቃት መቋቋም ይቜላሉ። በተጚማሪም ዚተለያዩ ነገሮቜ በአንድ ላይ መኖር እንደውበት መታዚት ያለበት ጉዳይ ነው። ኹዚህ ስንነሳ አንድ ብሄሚ-ሰብ ራሎን ገንጥዬ ልውጣ ቢል ሊያድግ አይቜልምፀ ዹሚመኘውንም ነገር ሊያገኝ አይቜልም። በአንድ ወጥ አስተሳሰብ ብቻ ስለሚዋጥ አዳዲስ ነገሮቜን ሊፈጥር ወይም ኹሌላው ሊማር አይቜልም። ዹሰውን ልጅ ታሪክ ስንመለኚት አንዱ ኹሌላው በመጋባትና በመዋለድ ዚማሰብ አድማሱን እያሰፈና አዳዲስ ዹአኗኗር ስልት እያዳበሚ ነው እዚህ ደሹጃ ለመድሚስ ዚበቃው። በመሆኑም አንዳንድ ኀሊት ነን ባዮቜ ዚሚያነሱት፣ „ይህ ዹኔ ብቻ ነው“፣ „አትድሚሱብኝ“፣ „በክልሌ ተወስኜ መኖር እፈልጋለሁ“  ዹሚለው አባባል ዚመጚሚሻ መጚራሻ ራሱ ተገንጣዩን ነው ዚሚጎዳው።

ኹዚህ ስንነሳ ያለን አማራጭ አንድ ነገር ብቻ ነው። ኃይልን አሰባስቊ ታላቅና ዚተኚበሚቜ አገር መገንባት። ዚሳይንስና ዹቮክኖሎጂ ባላቀት መሆን። ትላንትናና ዛሬም በዓለም አቀፍ ደሹጃ ዹሚደሹገው ትግል በዚህ ላይ ነው። ሁሉም በአንድ አገር ዹሚገኝ ዚብሄሚ-ሰብ ኃይል በዹፊናው እታገላለሁ ዹሚል ኹሆነ ዚግዎታ ለውጭ ኃይሎቜ መሳሪያ ነው ዚሚሆነው። ዚተዳኚመና ዚተሰበጣጠሚ ኃይል ለውጭ ኃይሎቜ ማመስ ያመቻል። ስለዚህም አንዳንድ ኃያላን መንግስታት ኹጎናቾን ይቆማሉ ብሎ ማመን ዚዋህነት ነው። ይህንን ወይም ያኛውን ተንቀሳቃሜ ኃይል ዚሚደግፉት ለመበጥበጥ እንዲሚያመቻ቞ው በማመን እንጂ ዚአንድን ብሄሚ-ሰብ ነፃነት በመሻት አይደለም።

ኹዚህ ባሻገር በተለይም ለአንድ ኢትዮጵያና ብሄራዊ ነፃነት እንታገላለን ዹሚሉ ኃይሎቜ ዕድላ቞ውንና ዕምነታ቞ውን ኚኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ማገናኘት አለባ቞ው። በአንዳንዶቜ ዹሚነፍሰው ኚአሜሪካ ውጭ ምንም ነገር ማድሚግ አንቜልም ዹሚለው አስተሳሰብና ቅስቀሳ ኚሳይንስ ውጭና ታሪኚ-ቢስ አባባል ነው። ዚአንድ አገር ዕድል ሊወሰን ዚሚቜለው በዚያው በአገሩ ህዝብና በአገሩ ዹምሁር ኃይል ብቻ ነው። አስር ሺህ ኪሎ ሜትር ርቆ ዹሚገኝን ኃይል ዘመዮ ነው፣ ኹጎኔም ዹቆመ ነው እያሉ መጥራት፣ እባክህን አገሬን ዹጩር አውድማ አድርግልኝ ብሎ እንደመጋበዝ ይቆጠራል። ወደ ስልጣኔና ወደ ህብሚ-ብሄር ግንባታ ዚሚያመራው ትክክለኛው መንገድ አይደለም። ስለዚህም በራሳቜንና በህዝባቜን ላይ ኹፍተኛ ዕምነት እንዲኖሚን ያስፈልጋል።

ዚኢኮኖሚ ጥያቄና አፈታት ቜግር ጉዳይ!

በማንኛውም አገር ውስጥ ኚፖለቲካና ኚዲሞክራሲ ባሻገር ዚኢኮኖሚ ጥያቄ ወሳኝ ሚናን ይጫወታል። ፖለቲካና ዲሞክራሲ ጣራና ግድግዳ ሲሆኑ፣ ኢኮኖሚ መሰሚት ነው። በአሾዋ ላይ ዚተገነባ ቀት ዘላቂነት ዹሌለውን ያህል፣ በፀና ዚኢኮኖሚ መሰሚት ላይ ያልተገነባ አገር ሁልጊዜ በውዝግብ ዓለም ይኖራል። ስለዚህም ለአንድ አገር ዘላቂነትና ተቻቜሎ መኖር ዚግዎታ ዚኢኮኖሚ ጥያቄ ቁልፍ ቊታን ይይዛል።

በብዙ ዚሶስተኛው ዓለም አገሮቜ፣ በተለይም በአፍሪካ ውስጥ ያለው ትልቁ ቜግር ዚኢኮኖሚን መሰሚታዊ ቊታ በቅጡ አለመሚዳት ነው። ይህ ቜግር ዹተፈጠሹውና ዹሚፈጠሹው አብዛኛዎቜ ዚአፍሪካ መንግስታት፣ ኢትዮጵያንም ጚምሮ ስለሰው ልጅ ያላ቞ው ግንዛቀ እዚህ ግባ ዚሚባል አይደለም። በተጚማሪም ስለ አገርና ስለ ህብሚተሰብ ምንነት ትርጉም ዚተሚዱ አይመስሉም። በመሆኑም አንድ አገር እንዎት ደሹጃ በደሹጃ መገንባትና ህብሚተሰቡ እርስበርሱ መያያዝ እንዳለበት እንደመሰሚታዊ ጉዳይ ዹተወሰደ አይደለም። አብዛኛዎቹ ዚአፍሪካ መንግስታት፣ ኢትዮጵያንም ጚምሮ ዚህዝቊቻ቞ው አልኝታ ሳይሆኑ ዹወጭ ተላላኪና በሪሞርኪ ዹሚጠመዘዙ ነው ዚሚመስለው እንጂ ታሪክን ለመስራት ዚተኮተኮቱ አይደሉም።  በዚህም ምክንያት ዚአፍሪካ መንግስታት ኹዓለም አቀፍ ኩባንያዎቜ ጋር እጅና ጓንቲ በመሆን ዚአህጉሪቱን ሀብት እዚዘሚፉና ህዝቡን እያደኞዩት ነው።

በመሆኑም ዚአፍሪካ መንግስታቱም ሆነ ኢሊቱ ስለኢኮኖሚ ትርጉም ያላ቞ው ግንዛቀ እጅግ ደካማ ነው። አብዛኛዎቻቜን በኒዎ-ክላሲካል ኢኮኖሚክስ፣ በሚክሮና በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዹሰለጠን በመሆናቜን በአንድ አገር ውስጥ እንዎት ህብሚተሰብአዊ ሀብት ተፈጥሮ በስነስርዓት ለህዝቡ እንደዚአስተዋፅዖውና እንደዚደሚጃው እንደሚኚፋፈል ግልጜ በሆነ መልክ ዚተሚዳን አይደለንም። ዚማክሮና ዚሚክሮ ኢኮኖሚክስ መጜሀፎቜን ላገላበጠ ስለአገርና ስለህብሚተሰብ ግንባታ ዚሚያወሩት ነገር ምንም ዚለም። ካፒታሊዝም መቌ እንደተጀመሚ፣ ለምንስ በተወሰነ አካባቢ ብቻ ማደግና መስፋፋት እንደቻለ፣ በምንስ ውስጣዊ ህጎቜ እንደሚሰራ አያስሚዱም። በማክሮ ኢኮኖሚና በሚክሮ ኢኮኖሚ አመለካኚት ሁሉም ነገር ያለና ዹተሰጠ(given) ስለሆነ ዚህብሚተሰብን ዕድገት ደሹጃ በደሹጃ አያሰቀምጥም። ኹዚህም በላይ ለምሳሌ ምርትን ለማመሚት ዚሚያገለግሉ ነገሮቜ ወይም ሪሶርስ በተቆጠበ(Scarce) መልክ እንደሚገኙ ሲያወሳ፣ በተለይም ካፒታል  በሶስተኛው ዓለም አገሮቜ በብዛት አይገኝም ይለናል። ስለዚህም ይላል፣ ዚሶስተኛው ዓለም አገሮቜ ካፒታል በብዛት ኚሚገኝባ቞ው ኚኢንዱስትሪ አገሮቜ ማስመጣት እለባ቞ው። እዚህ ላይ ካፒታል ሲል ዚገንዘብ ወይስ ዚፊዚካል መሆኑን ግልጜ ባይሆንም፣ ሁለቱንም ብንወስድ ዹሰው ልጅ ዚማሰብ ኃይልና ዚዕውቀት፣ እንዲሁም ዚዕድገት ደሹጃ ውጀቶቜ ና቞ው። ዹሁሉንም ዚካፒታሊስት አገሮቜን መነሻ ስንመለኚት ኹምንም ተነስተው ነው ዚተወሳሰበና በሳይንስና በቮክኖሎጂ ዹተመሰሹተ ኢኮኖሚ መገንባት ዚቻሉት። በሌላ አነጋገር ኚሳይንስና ኹቮክኖሎጂ ጋር አልተፈጠሩም። ወይም አምላክ ለእነሱ ብቻ ኹላይ አልወሚወላ቞ውም። በግለሰቊቜ ጥሚትና በሙኚራና በልምድ ነው ሳይንስና ቮክኖሎጂዎ ሊፈጠሩና ተግባራዊም ሊሆኑ ዚቻሉት። ስለሆነም ኹተፈለገና ታታሪነት ካለ በተለይም ዚፊዚካል ካፒታልን መፍጠርና ማሳደግ ይቻላል። ዚገንዘብ ካፒታል ደግሞ ኚኢኮኖሚው ዕድገት ጋር ዚሚሄድና ጥንካሬም ዚሚያገኝ ነው። ዚአንድ አገር ዕድገት በዶላርና በሌላ ዹውጭ ካሚንሲ ዹሚወሰን ሊሆን አይቜልም። ዚዶላርና ዚኊይሮ ሞኖፖሊ ብዙዎቜን ኀክስፐርቶቜን እያነጋገሚና በጥያቄ ውስጥም እዚተቀመጠ ዚመጣ ነው። ስለሆነም ዹውጭ ካሚንሲን እንደ አንዱ ዚምርት ኃይል አድርጎ መውሰድ ስህተት ነው። በተለይም ፕሮፌሰር ሶዲ እንደሚያስተምሩን፣ ታታሪነትንና ዚማሰብ ኃይል፣ ኃይልና(Energy) ማሜን ናቾው እንደ ሀብት መፍጠሪያና ማዳበርያ ዘዮ መወሰድ ያለባ቞ውና ትክክለኛውም መንገድ። በዚህም ምክንያት ማክሮና ሚክሮ ኢኮኖሚክስ ስለሀብት ዋናው ምንጭ፣ ማዳባሪያ ዘዎ፣ ስለሀብት ዕድገትና ክፍፍል ብዙም ዚሚነገሩን ነገር ዚለም። በጂዲፒ ዹሚገለጾው ዚኢኮኖሚ ዕድገት ስለ-ስራ ክፍፍል አስፈላጊነትና መዳበር፣ እንዲሁም ስለ ሳይንስና ስለ቎ክኖሎጂ፣ በተጚማሪም ስለኚተማዎቜ ዕድገትና በልዩ ልዩ ነገሮቜ መተሳሰር ዚሚያወራው ምንም ነገር ዚለም።

ኹዚህም በመነሳት ዚአንድ አገር ዚኢኮኖሚ ቜግር በነፃ ገበያ አማካይነት በአቅራቢና በጠያቂ መሀኹል ሊፈታ ይቜላል ዹሚለው በቁንጜል መልክ ዹቀሹበው አስተሳሰብ ለጀናማ ዚኢኮኖሚ ውይይትና አዲስ ሃሳብ ማፍለቅ ኹፍተኛ ቜግር ፈጥሮብናል። እንደሚታወቀው ዚኢኮኖሚክስ ዕውቀት እንደ ተፈጥሮ ሳይንስ፣ ፊዚክስ፣ ኪሜስትሪና ባይሎጂ ዚመሳሰሉት፣ ተፈጥሮን በመመልኚትና በመመርመር፣ አንዲሁም በማጥናት ዚተደሚሰበትና ዚሚደሚስበት ዕውቀት ሳይሆን፣ ዚአንድን ህብሚተሰብ ዹአወቃቀር ስርዓት በመመልኚት ዚዳባሚ ነው። አንድን ህብሚተሰብ ለማጥናት፣ በምን ነገሮቜ ላይ ቆሞ ነው ዚሚንቀሳቀሰው፣ ዚስራ ባህሉስ ምንድነው ለሚለው በምዕራቡ ዚፍልስፍናና ዚህብሚተሰብ ሳይንስ ዘንድ በርዕዮተ-ዓለም ደሹጃ ዚተለያዩ ዹአተናተን ዘዎዎቜ አሉ። ዚተለያዚ አመለካኚትና ዚፍልስፍና መሰሚት ያላ቞ው ዚህብሚተሰብ ሳይንስ ተመራማሪዎቜ ህብሚተሰብአ቞ውን በተለያዚ መነጜር ነው ዚሚመለኚቱት። በዚህም ዚተነሳ በተለይም ኢኮኖሚክስ በኹፍተኛ ደሹጃ በርዕዮተ-ዓለም ዹተወጠሹና ዚታጠሚ በመሆኑ ዚትኛው ነው ትክክለኛው ለሚለው ኹፍተኛ መፈላጥ እዚተካሄደ ነው። አንድ በእርግጥ ማለት ዚሚቻለው ነገር፣ ዹኒዎ-ክላሲካል ወይም ዹኒዎ-ሊበራል አመለካኚት ለጊዜው በአሞናፊነት በመውጣት ህብሚተሰቊቜን እያተሚማመሰ ነው። ዹኒዎ-ክላሲካል መተንተኛም ዘዮ ዚአንድን ህብሚተሰብ ውስጣዊ ህጎቜና ዚዕድገት ደሚጃዎቜና፣ በልዩ ልዩ መስኮቜና ዚህብሚተሰብ ክፍሎቜ መሀኹል ያለውን መተሳሰሚና ጥገኝነት በመውሰድ ሳይሆን ሞዮል ለማውጣት ዹሚሞክሹው በክስተት(Phenomenon) ላይ ብቻ በመመርኮዝ ነው። እኛም ሳናውቀው ዹዚህ ርዕዮተ-ዓለም ሰለባ በመሆን ግራ ተጋብተናል። እጅግ ዚሚያሳዝነው ነገር ሌሎቜ ግልጜና ለህብሚተሰብ ግንባታ ዚሚያገለግሉ ግሩም ግሩም ዚኢኮኖሚክስና ዚዕድገት መጜሀፎቜና ዕውቀቶቜ እያሉ አብዛኛዎቻቜን ለምን ጭንቅላታቜን ለተቀደሰው ነገር እንደተጋሚደ በፍጜም አይገባኝም። ልክ እንደ ሃይማኖት ወይም እንደኮሙኒስት ርዕዮተ-ዓለም አንድ አመለካኚት ብቻ ይዘን ወደፊት መሞምጠጡ ለዕውነተኛ ምሁራዊ ክርክር ዕንቅፋት ሆኗል ማለት እቜላለሁ።

ያም ሆነ ይህ ኚእነ አዳም ስሚዝ በኋላ ዹፈለቀው ዚገበያ ኢኮኖሚ ትምህርትና አስተሳሰብ እያንዳንዱን ህብሚተሰብ በተናጠል ወስዶ መመልኚት፣ መመርመርና ማጥናት ሳይሆን አንድ ለሁሉም አገሮቜ ሊያገለግል ዚሚቜል ዓለም አቀፋዊ ህግ አለ ወደሚለው ተቀባይነት ወዳገኘ ዶግማ ውስጥ ኚቶናል። ይህ ዐይነቱ አስተሳሰብና ዕምነት ደግሞ ልክ ዚካቶሊክ ሃይማኖት ኚክርስቶስ ልደት በኋላ ኚስድስተኛው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ እስኚ 15ኛው ክፍለ-ዘመን ድሚስ ዚአውሮፓን ህዝብ ጭንቅላት ወጥሮ በጹለማ ውስጥ እንዲኖር እንዳስገደደው ሁሉ፣ ዹኒዎ-ክላሲካል ወይም ዹኒዎ-ሊበራል አመለካኚት በመስፋፋቱ ብዙ ዚሶስተኛው ዓለም ህዝቊቜ በጹለማ ዓለም ውስጥ እንዲኖሩ ተገደዋል። በጥያቄ ውስጥ ሊገባ እንደማይቜል ዚእግዚአብሄር ቃል አድርገው አምነው ተቀብለውታል። ዕውነትን ኚውሞት እንዳይለዩ መንገዱ ሁሉ ጠፍቶባ቞ዋል።  ስለዚህም አገሮቜ በሙሉ ካሉቡትና ኚሚኖሩበት ተጚባጭ ሁኔታ ባሻገር ይህንን በምዕራቡ ዓለም ዹተወሰነ አመለካኚት ባላ቞ው ዚኢኮኖሚክስ አዋቂ ነን በሚሉ ዚዳባሚውን ኚሳይንስ ውጭ ዹሆነውን ዚኢኮኖሚክስ ትምህርት እንዲቀበሉና ተግባራዊ እንዲያደርጉ ተገደዋል።

ዚኢኮኖሚክስን ዕውቀት በሚመለኚት ኚጥንቱ ዚግሪክ ስልጣኔ ጀምሮ ውይይት ዚተደሚገበት ነው። ኢኮኖሚክስ ዹሚለው ጜንሰ-ሃሳብ ዹመነጹው ቀተሰብን ማስተዳደር(House Hold Management) ኹሚለው ነው። ይሁንና ፕላቶን በሪፑብሊክ መጜሀፉ ውስጥ ስለ ስራ-ክፍፍልና ስለንግድ አስፈላጊነት አስፍሯል። ዚስራክ-ፍፍልም መኖር ዚግዎታ አንድን ህብሚተሰብ እንደሚያቀራርብና አስፈላጊም እንደሆነ ያወሳል። ይህም ማለት ኚንግድ በፊት ዚሰራ-ክፍፍልና ምርት መቅደም አለባ቞ው። ሲመሚት ብቻ ነው ዚገበያ ልውውጥ ሊኖር ዚሚቜለው። ለማምሚት ደግሞ ዚግዎታ ዚምርት መሳሪያዎቜ መኖር አለባ቞ው። ይህ ሁኔታ በሌለበት አገር ውስጥ ስለምርትና ስለንግድ ልውውጥ ማውራት አይቻልም። ይሁንና ደግሞ ስለኢኮኖሚ በሚወራበት ጊዜ እንዲያው ለማምሚት ተብሎ ዚሚመሚት ጉዳይ አይደለም። ኢኮኖሚ ዹሚገለጾው ዹሰው ልጁ ኚተፈጥሮ ጋር በሚያደርገው ግኑኝነት፣ በማሰብ ኃይሉ በተፈጥሮ ውስጥ ያሉትን ነገሮቜ አይ እያወጣ ቅርጜና መልክ እዚሰጠ ይጠቀማል፣ ዚእርሻ ሰብል ደግሞ ኹሆነ እዚዘራና እያመሚተ ዚራሱን ምንነት ይገልጻል። ስለዚህም ዹሰው ልጅ ኚእንስሳ ዹሚለዹው በማሰብ ኃይሉ ተፈጥሮን ለራሱ መጠቀሚያ ሲያደርግና፣ በዹጊዜው ደግሞ ኑሮውን እያሻሻለ ሲሄድ ብቻ ነው። በሌላ አነጋገር ዹሰው ልጅ ኚተፈጥሮ ጋር ግኑኝነት ሲያደርግና ሲሰራ ዚማሰብ ኃይሉንና ሰውነቱን በመጠቀም እስኚተወሰነ ደሹጃ ድሚስ ተፍጥሮን ይለውጣታልፀ ወይም ደግሞ በተፈጥሮ ላይ ተፅዕኖ ያሳድራል። በተፈጥሮና በሰው ልጅ መሀኹል መደጋገፍ ሲኖር፣ ተፈጥሮ ሳትሆን ዹሰው ልጅ ለመኖር ሲል ሙሉ በሙሉ ዚሚመካው በተፈጥሮ ላይ ብቻ ይሆናል። ስለዚህም ኢኮኖሚ ተራ ዚማምሚትና ዚልውውጥ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ጠቅላላው ዹሰው አካል እንቅስቃሎና ዚማሰብ ኃይል ዚሚገለጜበት፣ ዹሰው ልጅ ራሱን ዚሚያሻሜልበትና ኚአንድ ዚዕድገት ደሹጃ ወደ ሌላ ዚሚሞጋገርበት ነው። ኢኮኖሚያዊ ድርጊት ሜታቊሊካል ነው። ይህም ማለት ኢኮኖሚ ሁለንታዊ ነው ማለት ነው።

ኹዚህ ስንነሳ ዹሰው ልጅ እንደ ማሀብሚሰብ ሲደሚጃና ሲያመርት፣ እንዲሁም ደግሞ ዚስራ ክፍፍል ሲዳብር ዚግዎታ መገበያዚት አስፈለገ። እንደሚታወቀው ማንኛውም ዚህብሚተሰብ ክፍል ሁሉንም ማምሚት ስለማይቜል፣ ሌላው ሌላ ዐይነት ምርት ካመሚተው ጋር ልውውጥ ለማድሚግ ሲል ገበያ ዚሚባለው ኢንስቲቱሜን ተፈጠሚ። በመጀመሪያው ዹነበሹው ዹዕቃ በዕቃና ዚምርት በምርት ልውውጥ በገንዘብ አማካይነት በመተካት ለገበያ ኢኮኖሚ መዳበር ልዩ ዕምርታና ገጜታ ሰጠው። ይሁንና ግን በመጀመሪያው ወቅት ዹነበሹው ዚገንዘብ ዐይነት አመቺ ስላልነበር፣ በቀላሉ ሊሜኚሚኚር ዚሚቜል ኚመዳብ፣ ኚብርና ኹወርቅ ዚተሰሩ ዚገንዘብ መለዋወጫ ዘዎዎቜ ተፈጠሩ። ዚገበያ ኢኮኖሚ እዚዳበሚና እዚተወሳሰበ ሲመጣ ወርቅም ሆነ ብር እንደልብ ይገኙ ስላልነበር ዚገበያ ዕድገትና ንግድ ወደ ሚቀዘቅዝበት ሁኔታ ተፈጠሚ። በ17ኛው ኹፍለ-ዘመን መጚሚሻ ላይ በወርቅ ዹተደገፈና በወርቅ ሊለወጥ ዚሚቜል ዚወሚቀት ገንዘብ ማተም አስፈላጊ ሆነ። ይህ ዐይነቱን በወርቅ ላይ ዹተደገፈ ዚገንዘብ ዐይነት ኹ1900 ዓ.ም ጀምሮ አባዛኛዎቹ ዚኢንዱስትሪ አገሮቜ ተግባራዊ በማድሚግ ለንግድ ልውውጥና መስፋፋት ይጠቀሙበት ጀመር። ኚመጀመሪያው ዓለም ጊርነት ጀምሮ በወርቅ ዕጥሚት ዚተነሳ በወርቅ ላይ ዹተደገፈ ዚገንዘብ ልውውጥ ኹቀሹ በኋላ እንደገና ደግሞ በ1930ዎቹ ጀምሮ ለጊዜው ተግባራዊ ኹሆነና ኹፈሹሰ በኋላ፣ ዚመጚሚሻ መጚሚሻ በ1944 ዓ.ም በብሬተንስ ውድስ ስምምነት አማካይነት በኢንዱስትሪ አገሮቜ ውስጥ፣ በተለይም ዹውጭ ገበያን በሚመለኚት በወርቅ ላይ ዹተደገፈ ዚገንዘብና ዚንግድ ልውውጥ ተቀባይነትን አገኘ። በ1971 ዓ.ም ይህ ስምምነት በመፍሚስ፣ ኚዚያን ጊዜ ጀምሮ በዓለም አቀፍ ደሹጃም ሆነ በኢንዱስትሪ አገሮቜ ዋናው መገበያያው ዶላርና ኊይሮ ና቞ው። ይህም በዕምነት ላይ ብቻ ዹተመሰሹተ ነው እንጂ ኚበስተጀርባው በምንም ነገር ዹተደገፈ አይደለም።

ይህንን ዚዘሚዘርኩት ለምንድነው? በታሪክ ውስጥ በጣም ጥቂት አገሮቜ ካልሆኑ በስተቀር አብዛኛዎቹ አገሮቜ እስኚተወሰነ ደሹጃ ድሚስ ዚገበያን ኢኮኖሚ አዳብሚዋል። ዚስራ-ክፍፍልም ነበራ቞ው። ይሁንና ግን በሁሉም አገሮቜ ካፒታሊዝም ሊዳብርና እንደስልተምርት ሊወጣ አልቻለም። በጣም ጥቂት ዹሆኑ ዚምዕራብ አውሮፓ አገሮቜ፣ በመጀመሪያ እንግሊዝ፣ ቀጥሎ ፈሚንሳይ፣ ጀርመንና አሜሪካ፣ ዹኋላ ኋላ ደግሞ ጃፓን በመንግስት ዹተደገፈ ፖሊሲ ተግባራዊ በማድሚግ ካፒታሊዝምን ወይም ደግሞ በሳይንስና በቮክኖሎጂ ላይ ዚተመሰሚተ፣ እጀግ ዚተወሳሰበ ዚውስጥ ገበያ ማዳበር ቜለዋል። ይህንን መንገድ ያልተሚዱና ተግባራዊ ማድሚግ ያልቻሉ ዚአፍሪካ አገሮቜ ወደ ንጹህ ዚጥሬ-ሀብትና ዚእርሻ አምራቜነት በመለወጥ ወደ ውስጥ አንድ ወጥ ዹሆነ ማህበሚሰብና ህብሚተሰብ መመስሚት አልቻሉም። በተለይም በትምህርት ቀት ውስጥ ዚተስፋፋው ዓለም አቀፋዊ ዚስራ-ክፍፍል ዹሚለው ዚኢኮኖሚክስ ትምህርትና፣ በዚህ አማካይነት እያንዳንዱ አገር ቢሰለጥን ኢኮኖሚውን ያሳድጋል፣ ህዝቡም ተጠቃሚም ይሆናል ተብሎ ስለሚሰበክ፣ ብዙዎቜ ወጣት ተማሪዎቜ በዚህ ዚተሳሳተ ዶግማ በመመራት አገሮቻ቞ውን መቀመቅ ውስጥ መክተት ቻሉ። ዛሬ በብዙ ዚአፍሪካ አገሮቜ ውስጥ ዚሚታዚው ድህነትና ዚኢኮኖሚ መዝሚክሚክ፣ ዚኚተማዎቜ በዕቅድ አለመሰራትና ህዝቡ በዘፈቀደ መኖር ኚሳይንስ ውጭ ዹሆነ ዚኢኮኖሚክስ ትምህርት በመስፋፋቱ ነው።

በዚህ መሰሚት ኹ1950ዎቹ ጀምሮ በአፍሪካ ምድር ዚተቋቋሙት ዚምትክ ኢንዱስትሪ ተኚላዎቜ(Import Substitution Industrialization)  ውጀታማ ያልሆኑት ኚተሳሳተ ስሌትና፣ በገበያ ኢኮኖሚ ብቻ ህብሚተሰብአዊ ሀብት ይፈጠራል፣ ኢኮኖሚውም ያድጋል ኹሚለው ኢ-ሳይንሳዊ አመለካኚት በመነሳት ነው። ዚአውሮፓን ዚኢኮኖሚና ዚህብሚተሰብ ግንባታ በቅጡ ላጠና ግን ዚገበያ ኢኮኖሚ ቀሰ በቀስ ተግባራዊ መሆን ዚቻለው በመንግስታት አማካይነት ኚተማዎቜና መንደሮቜ ኚተነገቡና ህዝቡ መሰባሰብ ኹጀመሹ ወዲህ ነው። ይህ አዲስ ዹተፈጠሹው ሁኔታ ለዕደ-ጥበብ ስራና ለንግድ ማበብ በሩን ሲኚፍት በዚያውም አማካይነት ቀስ በቀስ ዹሰው ልጅ ዚማሰብ ኃይል ይዳብራል። አዳዲስ ዹህንፃ አሰራሮቜና ስዕሎቜ፣ ድርማና ኊፔራ በመበልጾግ በአውሮፓ ህዝብ ጭንቅላት ውስጥ ልዩ ዚማሰብ ኃይል ይዳብራል። እነጋሊሊዪና ኮፐርኒኚስ፣ ኬፕለርና ባኮን፣ በኋላም ኒውተንና ጋውስ አንዲሁም ሪማን ዹዚህ አዲስ ዹተፈጠሹው ሁኔታ ውጀቶቜ ና቞ው። አካባቢዎቜና ሁኔታዎቜ ሲፈጠሩ ብቻ ዚሰዎቜ ዚማሰብ ኃይል በመዳበር ዚሳይንስ ግኝት መዳበርና መስፋፋት ቻለ። ቀስ በቀስም በሳይንስ አማካይነት ብቻ ካፒታሊዝም ቎ክኖሎጂዎቜን በማዳበር ዛሬ ዹምናዹውን ዚበላይነት መጎናፀፍ ቻለ።

ይሁንና ግን ካፒታሊዝም እንደስልተምርት በኹፍተኛ ደሹጃ ይንቀሳቀስ ዘንድ ዹግል ሀብት ወሳኝ ሚናን ቢጫወትም፣ በውድድር ዓለም ውስጥ ዚሚኚንፍ፣ በዹጊዜው ኢንቬስት ለማድሚግ ሪስክ ዚሚወስድና ትርፍ ለማካበት ዚሚጣደፍ ኚበር቎ያዊ ዚህብሚተሰብ ክፍል መኖር አስፈላጊ ነው። ዓላማውም ኹአጭር ጊዜ አንፃር ዹሚነደፍ ሳይሆን፣ ገበያ ውስጥ በተኚታታይ ኹቆዹና ዚመወዳደርር  ብቃቱን ማሳዚት ዚቻለ እንደሆን ቀስ በቀስ ግን ደግሞ በእርግጠኝነት ትርፍ ያተርፋል። በዚህም መሰሚት ኚአንድ ደሹጃ ወደሌላ በመሾጋገር አዳዲስ ቎ክኖሎጂዎቜን በመትኚልና ዚማምሚት ኃይሉን በማሳደግና በጥራት በማምሚት ገበያውን ወደ መቆጣጠር ያመራል። በዚህ መልክ በተለያዚ መስክ ዚተሰማሩ ካፒታሊስቶቜ በውድድር ዓለም ውስጥ በመክነፍ ሳያውቁት ሰፋ ላለ ገበያ መዋቀር ውስጠ-ኃይል ይሰጡታል። ኚተለያዩ ተጚባጭ ምርትን ኚማያመርቱ፣ እንደ ባንክ፣ ኢንሹራንስና ኚተለያዚ ዚንግድ መስክ ጋር በመቆላለፍ ካፒታሊዝም ሁለንታዊና ህብሚተሰቡን እንዲቆጣጠር ያደርጉታል። ካፒታሊዝም ኹዚህም በማለፍ ዓለም አቀፋዊ ባህርይ በመውሰድ ገበያንና ዚጥሬ-ሀብትን ወደ መቆጣጠር ያመራል። በራሳ቞ው ኃይል ሊቆሙ ዚማይቜሉ ህብሚተሰቊቜን በመቆጣጠር ዚጥሬ-ሀብትና ዚእርሻ ምርት አምራ቟ቜና አቀባዮቜ እንዲሆኑ ያደርጋ቞ዋል። በዚያውም ቀጭጹው እንዲቀሩ በማድሚግ አሚማመዳ቞ውን ይወስናል። ዚካፒታሊዝምን ሁለንታዊነትና እንቅስቃሎ  ለመሚዳት ኚታቻ ዹሰፈሹውን ግራፊክ መመልኚቱ ተቀራራቢ ስዕል ይሰጠናል።

 

 

ኹ1950ዎቹ ዓ.ም ጀምሮ ዚተሳሳተ ፖሊሲ መኹተል ዚጀመሩት ሁሉም ዚአፍሪካ አገሮቜ እዚያው በዚያው በድህነት ህዝባ቞ውን ዚሚያሰቃዩት ይህንን ዚአውሮፓውን ዚዕድገት ፈለግና ዚካፒታሊዝምን ምንነት ባለመሚዳት ነው። ኚምትክ ዚኢንዱስትሪ ተኹላ ጀምሮ፣ እስኚ ቀዚክ ኒድስና፣ ዹመዋቅር መስተካኚያ ፕሮግራም(Structural Adjustment Program(SAP)) ድሚስ በአፍሪካ ምድር ውስጥ ተግባራዊ ዚሆኑት ዚኢኮኖሚ ፖሊሲዎቜ በሙሉ ሀብትን ዚሚፈጥሩና ዕድገትን ዚሚያመጡ ሳይሆኑ፣ ድህነትን ዹሚፈለፍሉ ና቞ው። በአገራቜን ምድርም ኹ1993 ዓ.ም ጀምሮ ይህ ፖሊሲ ተግባራዊ በመሆን ድህነት በታሪካቜን ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ እንዲመሚት ሊደሹግ በቃ። በደሀና በሀብታም መሀኹል ኹፍተኛ ልዩነት እንዲፈጠር በማድሚግ ሰፊው ህዝብ እዚተገፋና እዚተሰቃዚ እንዲኖር ተደሚገ።

በአገራቜን ምድር ዛሬ ዹሰፈነው እጅግ ዚሚያሳዝንና ዹሚዘገንን ድህነት፣ ዚህዝባቜን አስኚፊ ኑሮ ኚግሎባል ካፒታሊዝም ደካማ አገሮቜን አቆርቁዞና አደህይቶ ኹማኖር ስትራ቎ጂ ተነጥሎ ሊታይ በፍጹም አይቜልም። ይህ ያልገባው፣ ወይም ገብቶት ለውይይትና ለክርክር፣ እንዲሁም ህዝብን ለማስተማር ዝግጁ ያልሆነ ሰው እንዲያው በደፈናው አገሬ አገሬ፣ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ እያለ ቢጮህ ዋጋ ዚለውም። ዝም ብሎ ዹሰውን ጆር ኹማደንቆር በስተቀር ዚሚፈጥሚው ነገር ዚለም። ይህ ግንዛቀ ውስጥ ኚገባ በመሰሚታዊ ነገሮቜ ላይ መነጋገር እንቜላለን። በዚህ ላይ መግባባት ኹሌለ በተለያዚ ቋንቋ ስለምንነጋገር ፊናቜንን እዚለዚን መታገል ይኖርብናል ማለት ነው።

ኹዚህ በመነሳት ኢኮኖሚስቶቜ ነን እያሉ እዚህና እዚያ እዚተሯሯጡ በተወሳሰበ ሞዮል ራሳ቞ው ግራ ተጋብተው ሌላውን ግራ ዚሚያጋቡ፣ ዹሰው ልጅ ሰለገበያና ስለግብይይት ኚማውራቱ በፊት ራሱን ስለመመገብ መጹነቅ እንዳለበት አያሰተምሩም። እንዎት ብዩ ነው ሆዮን ሞልቌ ዚማድሚው? ብሎ ራሱን መጠዹቅ እንዳለበት አይነግሩንም። እንደሚታወቀው መኪና ካላቀንዚን ወይም ካለኃይል ለመንቀሳቀስ ዹማይቾልውን ያህል ዹሰው ልጅም ለመንቀሳቀስና ለመስራት ዚግዎታ ምግብ ያስፈልገዋል። ምግብ ለሰው ልጅ ኃይል ሰጭ ነው። በምግብና በውሃ አማካይነት ብቻ ነው ህዋሶቹ ሊዳብሩና ሊንቀሳቀሱ ዚሚቜሉት። ስለዚህም ለአንድ አገርና ህዝብ ራስን በምግብ መቻል መሰሚታዊ ጉዳይ ነው። ይህ ኹፍተኛ ግንዛቀ ውስጥ መግባት መቻል አለበት። ይህ ሲሆን ብቻ ስለገበያ ኢኮኖሚና አወቃቀር መወያዚት ይቻላል። ዚዛሬውም ጥያቄ ዚገበያን ኢኮኖሚ ዹመቃወምና ለሱ ጠበቃ ሆኖ መታገል ሳይሆን፣ ይህ ወደ ርዕዮተ-ዓለምነት ዹተለወጠውን ዚገበያ ኢኮኖሚ በማጋለጥ አንዎት ጥበባዊ ዹሆነ ኢኮኖሚ መግንባት ይቻላል በሚለው ላይ ነው መኚራኚር ያለብን።

ስለ ማክሮና ሚክሮ ኢኮኖሚክስ ዹተማሹ በደንብ ተገንዝቊት ኹሆነ በማንኛውም መጜሀፍ ውስጥ ስለ አገርና ህበሚተስብን ስለመገንባት ጉዳይ በፍጹም አይወራም። በማክሮና በሚክሮ ኢኮኖሚክስ እመለካኚት አገርና ህብሚተሰብ በፍጹም አይታወቁም። ሁሉም ነገር ወደ ገበያነት ስለሚለወጥ ሁሉም ሰው ህልሙንና ምኞቱን በገበያ አማካይነት ብቻ ነው ተግባራዊ ዚሚያደርገው። ይህ ብቻ ሳይሆን ሚክሮና ማክሮ ኢኮኖሚክስ ስለፍጆታ አጠቃቀም፣ ስለሞኔተሪና ስለፊስካል ፖሊሲ ነው እንጂ ዚሚያወሩት ስለምርት ማምሚት፣ ስለ ሳይንስና ስለ ቮክኖሎጂ አስፈላጊነት አንዳቜም ቊታ አይነግሩንም። ዚሚክሮና ዚማክሮ ኢኮኖሚክስ ዋናው መሰሹተ-ሃሳብ ዚንግድ ልውውጥ ነው። ራሱ ዚኢኮኖሚክስ ፍልስፍና አባት በመባል ዚሚታወቀው አዳም ስሚዝ ዚሚያነሳ቞ው መሰሚታዊ ዹሆኑ ነገሮቜ አሉ። ይኾውም ዚስራ-ክፍፍልና ዚማሺነሪን አስፈላጊነት ነው። ቻርለስ ባቀጅ ዚሚባለው ዹ18ኛው ክፍለ-ዘመን ታላቅ ኢንጂነር ስለ ኢኮኖሚክስ ኩፍ ማሺነሪ በሚለው መጜሀፉ ውስጥ አጥብቆ ዚሚያነሳው ካለማሺን አጠቃላይና ሁለ-ገብ ዹሆነ ዚምርት እንቅስቃሎን ማካሄድ እንደማይቻል ነው። ማርክስና ሹምፔተርም ይህንን አስተሳሰብ ያሰምሩበታል። ካለ቎ክኖሎጂ ምጥቀት ሰለኢኮኖሚ ዕድገትና ስለሀብት ፈጠራ ማውራት አይቻልም። ስለዚህም ይላል ሹምፔተር፣ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እንደክንዋኔ መታዚት ያለበትና ኚሚዥም ጊዜ በኋላ ነው ተግባራዊ ሊሆን ዚሚቜለውና ሁሉንም ዚሚያዳርሰው። ለዚህም ደግሞ ዚኢኮኖሚን ውስጣዊ ህግ ማውቅ ያስፈልጋል። ኢኮኖሚያዊ ክንዋኔና ዕድገት ፊዚካላዊ፣ ኬሚካላዊና ባዮሎጂካል ክንዋኔ ዚሚያጠቃልል መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። ይህም ማለት አንድ ነገር በሀይል አማካይነት ብቻ ነው ኚአንድ ጥሬ ሁኔታ ወደ ፍጆታ ወይም ጠቀሜታነት ሊለወጥ ዚሚቜለው። በምርት ክንውን ውስጥ ፊዚካላዊና ኬሚካላዊ ለውጩጭ ይካሄዳሉ። ማንኛውም ነገር በምርት ክንውን ውስጥ ዚመጀመሪያውን ወይም ጥንታዊ ቅርጹን በማጣት ወደ ፍጆታነት በመለወጥ ዹሰውን ልጅ ፍላጎት ያሟላል ማለት ነው። ምርት በዹጊዜው በኹፍተኛ ደሹጃ ይመሚት ዘንድ ዹኃይል ማመንጚት ሁኔታና ዐይነት አዚተሻሻለና ብቃትን እያገኘ መምጣት ለኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ ነው። በሌላ አነጋገር በፊዚክስ፣ በኬሚስትሪና በባዮሎጂ ላይ ርብርቊሜ ኹሌለ ስለ ኢኮኖሚ ዕድገትና ክንዋኔ ማውራት አይቻልም። ሁሉም ነገር በፊዚክስ አማካይነት ብቻ ነው መዳበር ዚሚቻለው። መካኒካል እነርጂ፣ ዚሙቀትና ዚኀሌክትሪካል ኢነርጂ፣ መካኒክስ፣ ኊፕቲክና ፋይን መካኒክስ፣ እንዲሁም ኀሌክትሮኒክስ ዚፊዚክስ መሰሹተ-ሃሳቊቜና ዚኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ ነገሮቜ ና቞ው። ስለዚህም ካለተፈጥሮ ሳይንስ ስለኢኮኖሚና ስለ ዕድገት ማውራት በፍጹም አይቻልም። በተለይም በፊዚክስ አማካይነት ነው በአንድ አገር ውስጥ ዕውነተኛ ህብሚተሰብአዊ ሀብትን ማዳበር ዚሚቻለው።

ኹዚህ በላይ ኚተዘሚዘሩት መሰሹተ-ሃስባቜ በመነሳት እንዎት አድርገን ዚአገራቜንን ዚተወሳሰበ ቜግር መፍታት ይቻላል? ብለን መወያዚት አለብን። በመጀመሪያ ግን ዚኢትዮጵያን ህዝብ በሚያንገበግበው  መሰሚታዊ፣ በተለይም በምግብ ላይ አትኩሮ መስጠት ያስፈልጋል። ዛሬ ህዝቡን አላላውስም ብሎ አንቆ ዚያዘውን ዚኑሮ ውድነት ላይ በሚገባ መወያዚት አለብን። ዚቜግሩን ዋና ምክንያት ማወቅ አለብን።  ዚምግብ መሰሚታዊ ጥያቄ ሲፈታለት ብቻ ነው ህዝባቜን አገሩን አገሬ ብሎ ሊጠራ ዚሚቜለው። በጋራም እጅ ለእጅ ተያይዞ አገሩን መገንባት ዚሚቜለው።

አሁንም ኚታሪክ በመነሳት ዚአውሮፓውን ዚህብሚተሰብ ዕድገት ታሪክ ስንመለኚት በዚወቅቱ ዚነበሩት አገዛዞቜ ቅድሚያ ይሰጡ ዹነበሹው ዚምግብን ጥያቄ ለመፍታት ነበር ዚሚሯሯጡት። ኚዚያ በመነሳት ነው ቀስ በቀስ ወደሚቀጥለው ደሹጃ መተላለፍ ዚቻሉት። ይሁንና ግን ሌሎቜ ነገሮቜም እዚያው በዚያው ጎን ለጎን ይካሄዱ እንደነበር ግልጜ ነው። ዚነሱን ዚዕድገት ስትራ቎ጂ ስንመለኚት አካሄዳ቞ው ሁለ-ገብ(Holistic)ነበር። ዚገበያ ኢኮኖሚ እያሉ ዚተሯሯጡብት ወቅት አልነበሚም። በሌላ ወገን ግን ዚገበያን ኢኮኖሚ ክንዋኔ ኚውስጡ አጠቃላይ ዕድገት ነጥለው ያዩበት ጊዜ አልነበሚም። በጊዜው በምሁራን ዘንድ ይታወቅ ዹነበሹው ዚውስጥ ገበያ(Home Market) ዚሚባለው ፅንሰ-ሃሳብ ነበር። ይህም  ደግሞ ኚአጠቃላዩ ህብሚተሰብአዊ ክንዋኔና ዕድገት ተነጥሎ ዚሚታይ አልነበሚም።

ያም ሆነ ይህ በአገራቜን ውስጥ ዚምግብን ቜግር እንዎት መፍታት እንቜላለን? በሚለው ላይ ውይይት ማካሄድ ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ ዚዚካቲቱ አብዮት ይዞ ኚተነሳ቞ው ጥያቄዎቜ ውስጥ አንዱ ዹሆነውን ዚመሬት ለአራሹን ጥያቆና ሪሶርስን ዚመቆጣጠር ጉዳይ እንደመነሻ መውሰድ አንቜላለን። በመስሚቱ ዚዚያን ጊዜው ጥያቄ ትክክልል ዹሆነውን ያህል በነበሹው ዚፖለቲካ ትርምስ ምክንያት ዚተነሳ በትክክል ዹተመለሰ አይደለም። ይህም ማለት ገበሬው በቂ መሬት ማግኘት አለመቻሉ ብቻ ሳይሆን በተለያዚ መንገድ ዚራሱን ምርት ተቆጣጣሪ መሆን አልቻለም። በተጚማሪም ዚመሬት ለአራሹን ጥያቄ በትክክል ተግባራዊ ለማድሚግ ዚሚያስፈልጉት ዚኢንስቲቱሜን፣ ዚማ቎ሪያልና ዚገንዘብ ድጋፍ በሚገባ አልተዘጋጀም ነበርፀ ወይም ደግሞ በጊዜው ዚፖለቲካ ትርምስና ግብግብ ዚተነሳ እነዚህ ነገሮቜ ደሹጃ በደሹጃ እንዎት መፈታት እንዳለባ቞ው ለማጀን ጊዜ አልተገኘም ነበር ማለት ይቻላል።  ወያኔ/ኢህአዎግ ስልጣን ኚያዘ በኋለ ይህንን ቜግር ለመፍታት ዹወሰደው እርምጃ ዚገበሬውን ዚማምሚት ኃይል ዚሚያዳክም ነበር። በመጀመሪያው ወቅት ገበሬው በበቂው እያመሚተ ገበያ ላይ አምጥቶ ሊሞጥ ሲል ኹውጭ በመጣና በርካሜ በሚሞጥ ስንዎና በቆሎ ጋር ይጋፈጥ ስለነበር ምርቱን ማፍሰስ ብቻ ሳይሆን፣ ዚምርቱንም ሂደት ወደማቀዝቀዝ ተገፋ። ኹዚህ በላይ ደግሞ ቡናና ጚአት ነው ዚሚያዋጣው እዚተባለ መወራት ስለተጀመሚ፣ አንዳንዱ ወደ ጚአት ተኹላ ላይ ተሰማራ። ዹተቀሹው ደግሞ ወደ አበባ ተኹላ አመራ። ድሮ ስንዎና ጀፍ ዚሚመሚትባ቞ው መሬቶቜ ለውጭ ገበያ ምንዛሪ በማለት ወደ አበባ ተኚላነት ተቀዚሩ። ይህ በእንደዚህ አንዳለ ገበሬውን በራሱ ቁጥጥር ስር ለማድሚግ ስትራ቎ጂ ዹቀዹሰው ዚወያኔ አገዛዝ በእርሻ ላይ ዹተመሰሹተ ዚኢንዱስትሪ ተኹላ በሚለው አጉል ፈሊጥ ገበሬውን በዕዳና በደንብ ባልተጠና ዘርና ማደባሪያ እንዲሁም ዚተባይ ማጥፊያ በመተብተብ ምርት በጥራትም ሆነ በብዛት እንዳይመሚት አደሚገ። ኹዚህ ባሻገር ተግባራዊ ባደሚገው ዹክልል ፖሊሲ ዚተነሳ በመጀመሪያው ወቅት በኊሮሞ ዹነፃ አውጭ ግንባርና (OLF) በራሱ በወያኔ ብዙ ገበሬዎቜ ያለሙትን መሬት ለቀው እንዲሞሹ ተገደዱ። ዚተቀሩት በግፍ ተገደሉ። ይህ ዐይነቱ ጭፍን አካሄድ በኚተማዎቜ ዚህዝብ ቁጥርና አዳዲስ ዚአገልግሎት መስክ እንዲስፋፋ ሲያደርግና ሆቮል ቀቶቜ በብዛት ሲሰሩ በገጠሩና በኚተማ፣ በተለይም በአዲስ አበባ መሀኹል ያለው ዚዕድገት ሁኔታ መዛባትን ፈጠሚ። ዚአዲስ አበባ ኹተማ ዚገጠሬውን ዚአራሜ ኃይል ሟጣጭ ብቻ ሳይሆን ሌሎቜ ሀብቶቜን፣ እንደ እርሻ ውጀት ዚመሳሰሉትን ዚሚጋራ ሆነ። በሌላ አነጋገር በተለይም በገጠሩ ህዝብ ላይ ዚሚመካው አዲሱ መጀ ሀብታም ኚገበሬው ሀብት በተለያዚ መልክ ዚሚጋራውን ያህል፣ ለሱ መልሶ በዕውቀት ዚሚክስበት ዘዮና ፍላጎት አልነበሚውምፀ ዚለውምም። በዚህም ምክንያት ዚተነሳ ሰፊው ገበሬ አሁንም እንደወትሮው በኢንስቲቱሜን ዹተደገፈ ጥናት፣ ዚማ቎ሪያልና ዚገንዘብ ድጋፍ ማግኘት አልቻለም። ለገበሬው እርሻ መዳኚም ሌላው ምክንያት ገበሬው ለዘሩ በውጭ አቅራቢዎቜ ጥገኛ እዚሆነ በመምጣትና ኚትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ ዚመጣውን ዹዘር ዐይነት እንዲያጣ መደሹጉም ጭምር ነው። ዚአሜሪካን አገዛዝ ዚሶስተኛውን ዓለም ህዝቊቜ በተለይም አፍሪካን ለመቆጣጠር ሲል በሞንሳቶ አማካይነት ዹዘር ዐይነቶቜ ስታንደርዳይድ መሆን አለባ቞ው በማለት ዚእርሻ ሚንስትሩ ላይ ጫና በማድሚግ ብሄራዊ ነፃነታቜንን ሙሉ በሙሉ ወደ መግፈፍ በማምራት ላይ ነው። በጊዜው ኚወያኔ ጋር ዹተቆላለፉ ግለሰቊቜና ኩባንያዎቜ ኹውጭ ዘር እያስመጡ ለገበሬው በመሞጥና ገበሬውን ሙሉ በሙሉ ጥገኛ በማድሚግ ላይ ነበሩ። ይህ ዐይነቱ ዚአትራፊነት ስልት በጠቅላላው ዚእርሻ ባህልና ወደፊት በምንገነባው ህብሚተሰብ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊያሳድር በቅቷል።

በመሰሚቱ ዚኢትዮጵያ ህዝብ መራብና መለመን አልነበሚበትም። እንደ ኢትዮጵያም ለእርሻ ዚሚስማማና ዚአስር ሺህ ዐመት ዕድሜ ዚሰብል ተኹላ ታሪክ ያለው አገር ዚለም። በአገራቜን ምድር ዚተለያዩ ዚስንዎና ዚጀፍ ዘሮቜ፣ ገብስ፣ አጃ፣ ማሜላና ዘንጋዳ፣ በቆሎ፣ አተርና ሜምቡራ፣ ባቄላና ቊለቄ፣ ቆጮና ድንቜ፣ ጎደሬና ወጭኖ እንዲሁም ልዩ ልዩ ዚስብል ዐይነቶቜና ፍራፍሬዎቜ ይበቅላሉ። በደንብ ኚታሰበበትና በሳይንስ ኹተጠና ተጚማሪ ዚሰብል ዐይነቶቜንም ማስፋፋት ብቻ ሳይሆን በብዛት ማምራት ይቻላል። ይህ ዐይነቱ ዚተለያዚ ዚሰብል ዐይነቶቜ በሚገኝበት አገርና፣ መሬቱ ለእርሻ በሚያመቜበትና ውሃ እንደልብ በሚገኝበት አገር ነው ህዝባቜን ኚሃምሳ ዐመት በላይ በዚአምስት ዐመቱ ዹሚለምነውና ዚሚራበው። ይህ ሁኔታ ዚግዎታ መለወጥ አለበት። ይህንን ለመለወጥ፣ ህዝብቻንን ለመመገብና፣ ዹተሹፈውንም ወደ ውጭ ለመላክና ምንዛሪ ለማግኘት፣ እንደገና መልሶ ለልማት ለማዋል ዚግዎታ ዚፖለቲካው ሁኔታ መለወጥ አለበት። ዚዛሬው ዚፖለቲካ አወቃቀር እስካልተቀዚሚ ድሚስ ወደ ሌሎቜ መሰሚታዊ ጉዳዮቜ መሾጋገር አንቜልም።

ዚዛሬው ዚፖለቲካ አወቃቀር ኹተለወጠና ሌላ ኃይል ስልጣን ቢይዝ መጀመሪያ ማድሚግ ያለበት በሞኖፖሊ ዚተያዙ ዚእህል እንቅስቃሎዎቜንና ንግዶቜን በቁጥጥር ስር ማዋል ነው። በሁለተኛ ደሚጃ፣ በእርሻ ተግባር ላይ ዚተሰማሩ ዹውጭ ዜጎቜን ማባሚርና መሬቱን ለኗሪው ህዝብ መልሶ መስጠት ግዎታ ነው። ዚእርሻ ተግባርን ማካሄድና መሬትን መንኚባኚብ ባህላዊ ስለሆነ ኹውጭ ዚመጡ ኢንቬስተር ነን ዹሚሉ ይህንን ጉዳይ ሊያሟሉ በፍጹም አይቜሉም። ኹዚህም ባሻገር ዹውጭ ኢንቬስተሮቜ ትርፋማ ናቾው በሚላቾው ሰብሎቜ ላይ ስለሚሰማሩ ለአገር ግንባታ ምንም አስተዋፅዖ ሊያበሚክቱ አይቜሉም። ለኩሙኒቲ ዕድገትና ለህብሚተሰብአዊ መተሳሰር እንቅፋት ብቻ ሳይሆኑ፣ በገጠር ውስጥ ኚእርሻ ጋር ዚተያያዘ ዹጎጆ ኢንዱስትሪ እንዳይቋቋምና እንዳይስፋፋ ያግዳሉ። ባጭሩ ዚኢትዮጵያ ህዝብ እንደህዝብና እንደ ህብሚተሰብ እንዳይተሳሰርና ጠንካራ አገር እንዳይገነባ ኹፍተኛ እንቅፋት ይሆናሉ። በሶስተኛ ደሚጃ፣ ማንኛውንም ለህብሚተሰቡ ዚሚያስፈልጉ ምግብና ምግብ ነክ ነገሮቜ ወደ ውጭ እንዳይላኩ ማድሚግ ነው። ኹዚህ ውጭ ደሹጃ በደሹጃ ዚገበያ ግልጜነት እንዲኖር አስፈላጊውን ዚመቆጣጠሪያ መሳሪያና ህግ ማውጣት ያስፈልጋል። በሌላ ወገን ደግሞ ኹውጭ ዚሚገቡ ኚአገሪቱ ምርት ጋር ዚሚወዳደሩ ምግብና ምግብ ነክ ነገሮቜን ማገድ፣ በኹፍተኛ ደሹጃ መቅሚጥ፣ ወይም ደግሞ መገደብ እጅግ አስፈላጊ ነው። አንድ አገር ዚራሷ በቂ ምርት እስካላት ድሚስ ዚግዎታ መግዛት አለብሜ ዹሚል ዚተፈጥሮ ህግ ዚለም። ኹዚህ ሌላ ኹውጭ ዚሚመጡ ምግቊቜ በሙሉ ኚኬሚካል ነፃ መሆናቾውን መቆጣጠርና፣ ለዚህ በእርሻ ሚንስተር ስር ዚሚተዳደር ላቊራቶሪ ማቋቋም ያስፈልጋል። በግል መንቀሳቀስ ዹሚፈልጉ ካሉም እነሱን በክሬድትና በምክር መደገፍ።

ዚእርሻውን መስክ ምርታማና ዚተለያዩ ስብሎቜን ለማምሚትና፣ ዚእርሻ ሰብሉም ለኢንዱስትሪው መስክ ዚጥሬ-ሀብት አቅራቢ እንዲሆን ዚግዎታ ዚእርሻ ሚንስትሩን በአዲስ መልክ ማዋቀርና፣ በዹክፍላተ-ሀገራቱም ተመሳሳይ ሚንስትሪዎቜ እንዲቋቋሙ ማድሚግ። ኹዚህ ጋር ተያይዞ ዚእርሻ መስኩን ምርታማ ለማድሚግ ዚግዎታ ለገበሬውና ለመሬቱ ዚሚስማማ ዚማሚሻና ዚእህል መሰብሰብያ ማሜኖቜንና መሳሪያዎቜን ማመሚቻ ፋብሪካ ማቋቋም እጅግ አስፈላጊ ነው። ዚገበሬውን ምርታማነት ማሳደግ ብቻ ሳይሆን ዚገበሬውን ድካም ማቃለል ዚሚቻለው በዹጊዜው ዚተሻሻሉ ዚማምሚቻ መሳሪያዎቜ ሲቀርቡለት ብቻ ነው። ኹዚህ ስንነሳ አልፎ አልፎ ካልሆነ በስተቀር ዚእርሻው መስክ ዚግዎታ በአግሮ ኢንዱስትሪ አማካይነት መካሄድ ዚለበትም። ይህ ዐይነቱ ዚአመራሚት ዘዮ ለእርሻ ባህል ፀር ዚሆነና፣ ኹንፁህ ትርፍ አንፃር ዚሚካሄድ በመሆኑ በጠቅላላው በመሬቱና በአካባቢው ላይ ኹፍተኛ ዹሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖሚዋል።

ኹዚህ መሰሚታዊ ጥያቄ ስንነሳ፣ ዚሚቀጥሉት ዚኢትዮጵያ ህዝብ አንገብጋቢ ጥያቄዎቜ፣ ንጹህ ውሃ ማግኝት፣ ኹጎጆ ቀት መላቀቅ፣ ኃይል ማግኘትና በገጠር ውስጥ አነስተኛና ማዕኹለኛ ዹህክምና ዘዎዎቜን ማስፋፋት ና቞ው። አብዛኛዎቹ ዹማዕኹለኛና ዚሚዥም ጊዜ ዕቅዶቜ ሲሆኑ፣ ደሹጃ በደሹጃ ሊመለሱ ዚሚቜሉና መመለስም ያለባ቞ው ና቞ው። መመለስም ይቜላሉ። እነዚህ ጥያዎቜ ካልተመለሱ ደግሞ ስለአገር ማውራት በፍጹም አይቻልም። በአገራቜን ምድር ዚሚገኙት ዚጥሬ-ሀብቶቜና ዹሰው ጉልበት ተጚምሮበት ኹላይ ዚተዘሚዘሩትን ነገሮቜ መመለስና መልክ ማሲያዝ ያስፈልጋል።  ለዚህ ደግሞ ኹፍተኛ ዹሆነ ዚሶሻል ፖለቲካ ግንዛቀ ያስፈልጋል። አንድ ህብሚተሰብ እንደሰውነታቜን በሚሊያርድ በሚቆጠሩ ዚነርብ ሲስተሞቜ መያያዝ እንዳለበት ሁሉ አንድም ህዝብ እንደማህበሚሰብና እንደህብሚተሰብ እንዲደራጅ ኹተፈለገ በቀጥታ በግልጜ መወሰድ ያለባ቞ው ነገሮቜ አሉ። አንድ አገር በማንኛውም ዹውጭ ኃይል ሊፈራና ሊኹበር ዹሚቾለው በውስጥ ባለው ዕድገትና መተሳሰር፣ ውብ በሆኑ ኚተማዎቜና መመላለሻዎቜ ሲተሳሰር ብቻ ነው። ይህንን መሚዳት ካልተቻለ ደግሞ እጅግ አስ቞ጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንገባለን ማለት ነው። ዛሬ መስመር ካልያዘ ዚዛሬ ሁለት መቶ ዐመትም ሊመለስ አይቜልም ማለት ነው።

ኹዚህ ተነስተን ወደ ሀብት ማዳበሪያ ወይም ማበልጞጊያ ዘዎዎቜ ስንመጣ ኚአውሮፓ ፈላስፋዎቜና ዚህብሚተሰብ ታሪክ ዹምንማሹው ቁም ነገር አለ። በመጀመሪያ ለአንድ አገር ዕድገት ጭንቅላትና ዚጭንቅላት መዳበር ዚሚይዙትን ኹፍተኛ ቊታ መገንዘብ ያስፈልጋል። ዚግሪክም ሆነ ዚአውሮፓ ፈልሳፋዎቜ ዚዕውቀትና ዚፈጠራ፣ እንዲሁም ዚሀብት ምንጭ ዋናው ነገር ዹሰው ልጅ ጭንቅላት ወይም ማይንድ ዚሚሉት ነው። ኹዚህ ጋር ተያይዞ ፍላጎት ወም ዊል(Will) ዚሚሉት ነገር አለ። እነዚህ ሁለት ነገሮቜ ሲጣመሩ ተራራንም መግፋት ይቻላል ይባላል።

ኹዚህ በተሹፈ በኢኮኖሚስቶቜ ዘንድ ዚሀብት ምንጭን በሚመለኚት ክርክር ተካሂዷል። ዚመጀመሪያዎቹ ኢኮኖሚስቶቜ፣ ፊዚዮክራትስ ተብለው ዚሚጠሩ እርሻንና ገበሬውን ዋናው ዚሀብት ምንጭ አድርገው ይወስዱ ነበር። በጊዜው ዚነበሩበት ሁኔታ ኹዚህ ርቀው እንዲያስቡና እንዲሄዱ ሊያደርጋ቞ው አልቻለም። ምክንያቱም በፊዚዮክራቶቜ ዘመን አብዛኛው ዚአውሮፓ ህዝብ በግብርና ዚሚተዳደርና በእርሻ ምርት ላይ ጥገኛ ዹሆነ ነበር።  በ17ኛው ክፍለ-ዘመን ብቅ ያሉት መርካንትሊስቶቜ ዚሚባሉት ኢኮኖሚስቶቜ ደግሞ ለአንድ አገር ዋናው ዚሀብት ምንጭ በውጭ ንግድ አማካይነት ዹሚገኝ ዹወርቅና ዚብር ክምቜት ነው ብለው ያምኑ ስለነበር፣ ብዙ ወርቅና ብር ለማግኘት ዹነቃ ዹውጭ ንግድ ፖሊሲ መካሄድ እንዳለበት ነገስታቱን ያማክሩ ነበር። በዚህ መሰሚት አንድ አገር ኚውስጥ ገበያዋን ስትኚላኚል ወደ ውጭ ደግሞ በብዛት መሞጥ አለባት። ይሁንና ግን መርካንትሊስቶቜ በዚህ ሳይወሰኑ ዚውስጥ ገበያን ለማስፋፋት መንግስታት ንቁ ዹሆነ ዚኢኮኖሚ ፖሊሲ መኹተል እንዳለባ቞ው ያስተምሩ ነበር። አነ አዳም ስሚዝ ብቅ ሲሉ፣ ዋናው ዚሀብት ምንጭ ስራ መሆኑ ተደሚሰበት። ማርክስ ይህንን በማስተካኚል፣ ስራ ዹዋጋ ምንጭ ሲሆን፣ ስራና ተፈጥሮ ወይም በተፈጥሮ ውስጥ ዹሚገኝ ነገሮቜ ተደምሹው ህብሚተሰብአዊ ሀብት መፍጠር ይቜላሉ ይለናል። ኹዚህ ወጣ ስንል ሳይንስ እዚዳበሚ ሲመጣ፣ ዹሰው ልጅ ጥሚት፣ ኃይልና ቮክኖሎጂ ዋናው ዚሀብት ማመንጫ ዘዎዎቜ ናቾው ወደሚለው ድምዳሜ ውስጥ ተደሚሰ። እነዚህ ሁሉ በዹጊዜው ኹነበሹው ተጚባጭ ሁኔታ በመነሳት ዚዳበሩ አስተሳሰቊቜና ዹሚደጋገፉ ና቞ው። አንደኛው ትክክል ነው፣ ሌላው ስህተት ነው ብለን መኚራኚር አንቜልም። ይሁንና ግን ሁሉም ቢሆን ለኢኮኖሚና ለህብሚተሰብአዊ ዕድገት ዚጭንቅላት ሚና ኹፍተኛ ቊታ ይሰጡታል። ገንዘብና ዚጥሬ ሀብት ተትሚፍርፎ ቢገኝም ካልታወቀበት እንደናይጄሪያና አንጎላ ድህነት መፈልፈል ይቻላል። ስለዚህም ትክክለኛ ዕውቀትና ፍላጎት ለአንድ አገር ዕድገት ወሳኝ ሚናን ይጫወታሉ ማለት ነው። ይህንን ዚሀብት አፈጣጠር ዘዮ በሚቀጥሉት ዲያግራሞቜ እንመልኚት።

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

ኹዚህ ስንነሳ ማኑፋክቱር በአንድ አገር ዕድገት ውስጥ ያለውን ቊታ ማስመር ያስፈልጋል። ዚማኑፋክቱር እንቅስቃሎና ዕድገት ኚእርሻ ጋር ሲወዳደር በጣም ኹፍ ያለ ብቻ ሳይሆን ዚማባዛት ኃይሉም ኹፍተኛ ነው። ኢኮኖሚስቶቜ እንደሚሉት እርሻ በማደባሪያና በማሜን ተደግፎ ስለሚሰራና፣ አንድ መሬትም በተደጋጋሚ ዚሚታሚስ ኹሆነ ውጀቱ እያደገ ሳይሆን እዚቀነስ(Deacreasing returns) ዚሚሄድ ነው። ዹማኑፋክተርን ትርጉም፣ ዹማደግና እንዲሁም ዚመስፋፋት ኃይል ዚተገነዘቡት ዚአውሮፓ መንግስታት ኹ14ኛው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ ኹፍተኛ ርብርቊሜ ያደሚጉት በእርሻ መስክ ላይ ሳይሆን በማኑፋክቱር መስክ ላይ ነው። ይህንን አትኮሮና ትክክለኛ ፖሊሲ ፕሮፌሰር ኀሪክ ራይነርት፣ ሀብታም አገሮቜ ለምን ሀብታም ሆኑ፣ ደሃ አገሮቜ ለምን ደሃ ሆነው እዚያው ቀሩ በሚለው መጜሀፋ቞ው ውስጥ እንደዚህ በማለት ያሰቀምጣሉ።“European observed early on that generalized wealth was found only in areas where agriculture was absent or only played a marginal role, and came to be seen as unintended by-product when many diverse branches of manufacturing were brought together in large cities. Once these mechanisms were understood, wise economic policy could spread wealth outside these few `naturally wealthy `areas.  Policies of emulation could, indeed, also spread wealth to formerly poor and feudal agricultural areas, but they involved massive market interventions. For laggard nations market interventions and wise economic policies could substitute the first wealthy states. We can further imagine that export taxes on raw materials and import taxes on finished products were originally means for increasing revenues in poor nations, but that a by-product of these measures was to increase wealth through the growth of domestic manufacturing capacity.This blend of purposes was already clear in England under Eduard III (1312-77)”   Prof. Erik S. Reinert, How Rich Countries Got Rich 
 and Why Poor Countries Stay Poor, London, 2007 P. 17)

ስለሆነም አንድ አገር እንድታድግ ኹተፈለገ ዚግዎታ ዚማኑፋክቱር አብዮት ማካሄድ አለባት። ይህንን ለማድሚግ ዚግዎታ ኚመጀመሪያውኑ በትላልቅ ኢንዱስትሪዎቜ ላይ መሚባሚብ ዚለባትም። እንደዚህ ዐይነቱንም አካሄድ ልንቆጣጠሚው ወደማንቜለው ቊታ ይወስደናል። በመጀመሪያ ደሹጃ ትናንሜና ማዕኹለኛ ኢንዱስትሪዎቜ ላይ መሚባሚብ ያለብን። እነዚህ ዚግዎታ በብሚታብሚትና በማሜን ፋብሪካ፣ ልዩ ልዩ ኢንዱስትሪዎቜን ዲዛይን በሚያደርጉ ኢንስቲቱሜኖቜ ወይም ኢንዱስትሪዎቜ መደገፍ አለባ቞ው። በመሰሚቱ በዕውቀት ላይ ዚተመሰሚቱ(Knowledge based) መሆን ሲገባ቞ው፣ በአገር ውስጥ ዚጥሬና ዹሰው ኃይል(Resource based) ዚሚንቀሳቀሱ መሆን አለባ቞ው። ኹዚህ ጋር በማያያዝ ያሉትን ኮሌጆቜ ወደ ቮኬሜናል ትምህርት ቀቶቜ በመቀዚር፣ ማንኛውም ተማሪ ኹ12ኛ ክፍል በኋላ በተኚታታይ በማንኛውም ቮክኖሎጂ ነክ ነገሮቜና ዚሳይንስ ስልጠናዎቜ አምስት ዐመት ሙሉ በተኚታታይ እንዲሰለጥን ማድሚግ። ኹዚህ በኋላ ዹፈለገው በቀጥታ ወደ ዩኒቚርሲት ይገባል፣ ሌላው ደግሞ ወደ ስራ መስክ ላይ ይሰማራል። በአጭሩ ትምህርቱ ተግባራዊና ፈጣሪ ዚሚያደርግ መሆን አለበት። ኚተለያዩ ዚኢኮኖሚ ዘርፎቜ ጋር መያያዝ አለበት። በዚኮሌጆቜና በዚቮኬሜናል ትምህርት ቀቶቜ በቂ መለማመጃዎቜና ላቊራቶሪዎቜ መቋቋም አለባ቞ው። በቂ መጻህፍት ቀቶቜ፣ በተለይም በአማርኛ ዚሳይንስና ዹቮክኖሎጂ መጻህፍት እዚተተሚጎሙ መቅሚብ አለባ቞ው። ለዚህ ዹሚሆን ሰፋና ትልቅ ዹምርምርና ዚመተርጎሚያ ላይብሚሪ ለብቻው መቋቋም አለበት። አስፈላጊው መጜሀፎቜ ኹውጭ እዚመጡ መተርጎም አለባ቞ው። በዚህ አማካይነት ብቻ ነው ዕወነተኛ ዕድገትን ማምጣት ዚምንቜለውፀ ሚሀብንና ድህነትንም ማጥፋት ዚሚቻለው።

ይህ መሰሹተ ጉዳይ ሲሆን፣ አሁን ያለውን ስራ-አጥ ህዝብና ወጣት በስራ ለማሰማራት ዘዎዎቜ መፍጠር ያስፈልጋል። እንደሚታወቀው ያሉት ኢንዱስትሪዎቜ ለዚህ ሁሉ ስራ ፈላጊ ዚስራ መስክ ሊፈጥሩ አይቜሉም። ያለው አማራጭ በኢንስቲቱሜን ዹሚደገፍ ኚስልጠና ጋር ዚሚያያዝ ዚስራ መስክ መክፈት ይቻላል።  ሰራተኛውን ወጣቱ በተለያዩ ሙያዎቜ በሳምንት ሁለት ቀን ኮርስ ይሰጣ቞ዋል። በተቀሹው ሶስት ቀን ፕራክቲካል ስራዎቜን በማዘጋጃቀትና በተቀሩት ኢንስቲቱሜኖቜ በሚዘጋጁት፣ እንደግንብ ስራ፣ እንደ መንገድ ስራ፣ እንድ ጋርደንና ዹዛፍ ተኚላዎቜ በመሰማራት ጊዜያ቞ውን ሊጠቀሙበትና ለህብሚተሰቡም ሀብት ሊፈጥሩ ይቜላሉ። ይህ ዐይነቱ ፕሮግራም በምግብ ለስራ በሚባል(Food for Work) ፈንድ ሲደገፍ፣ በዐይነትና በምግብ እንዲሁም በዘይትና በአንዳንድ ዚፍጆታ መልክ ይኚፈላል። በዚህ መልክ ኹ18 ዐመት ዕድሜ በላይ አንስቶ እስኚ 60 ዐመት ዕድሜ ድሚስ ያለውን ዹሰው ኃይል ማንቀሳቀስ ይቻላል። በእኔ ዕምነት ይህ መንገድ ብቻ ነው ያለንን ቜግር እንድንቀርፍ ዚሚሚዳን። ኹሁለተኛው ዓለም ጊርነት በኋላ እንደ ጀርመን ያሉ አገሮቜ ሰማንያ በመቶ ያህሉን ዚፈራሚሰውን ህንፃዎቻ቞ውንና ኢኮኖሚያ቞ውን በ15 ዐመት ውስጥ መልሰው መገንባት ዚቻሉት ህዝቡን ለስራ በማንቀሳቀስ እንጂ በተራ ዚገበያ ኢኮኖሚ አማካይነት አይደለም።

ይህንን ኚተመለክትን በኋላ ዚገበያ ኢኮኖሚ እያሉ ለሚጮሁት ግራ እንዳይጋቡ ዚአገሪቱን ኢኮኖሚ በሶስት መልኹ ማዋቀር ይቻላል። በመጀመሪያ ደሚጃ፣ ዚመንግስት ሚና ግልጜ ሆኖ መቀመጥ አለበት። ግለሰቊቜ ሊሳተፉባ቞ው በማይቜሉባ቞ው መስኮቜ ሁሉ ዚመንግስት ሚና ግልጜ ይሆናል። በሁለተኛ ደሚጃ፣ በጋርዮሜ ወይም በአክሲዮን መልክ ወይም በሌላ መልክ ሊቋቋሙና ለኢኮኖሚ ዕድገት አስተዋፅዖ ሊያደርጉ ዚሚቜሉ ዚአደሚጃጀትና አመራሚት ስልትን ማጥናት ይቻላል። በሶስተኛ ደሹጃ ግለሰብ ኚበር቎ዎቜ ወይም ኢንቬስተሮቜ ዚሚሳተፉበት ሁኔታ መዘጋጀት አለበት። ለዚህ ደግሞ ትናንሜና ማዕኹለኛ ባለሀብታሞቜን በዚትና በምን መስክ ላይ መሰማራት እንደሚቜሉ ምክር ዚሚስጥ ኢንስቲቱሜን መቋቋም አለበት። እዚህ ላይ መንግስት አጋዥ እንጂ ዹሚቀናቀናቾው መሆን ዚለበትም። በመንግስት ቁጥጥር ስር ዚሚካሄዱ ኢንዱስትሪዎቜም ሆነ ልዩ ልዩ ሀብቶቜ ዚህዝብ መሆናቾው በግልጜ መቀመጥ አለባ቞ው። መንግስት አገልጋይና ሁኔታዎቜን ዚሚያመቻቜ መሆን አለበት። ሀብት እዚፈጠሚም ትምህርት ቀቶቜ፣ ክሊኒኮቜ፣ ዹኃይል ማመንጫ ዘዎዎቻ፣ ዹውሃ ቧንባዎቜን፣ መንገዶቜንና መመላለሻዎቜ እንዲስፋፉና እንዲዳብሩ ድጋፍ መስጠት አለበት።

ይህንን ኚተመለኚትን በኋላ ይህንን ሁሉ እንዎት ፋይናንስ እናደርገዋለን ዹሚለው ጥያቄ ይነሳል። እንደሌሎቜ ዚአፍሪካ አገሮቜም በአገራቜንም ዚገንዘብንና ዚፋይናንስን ጉዳይ በሚመለኚት ትልቅ መወናበድ ይታያል። ይህም ዚሆነበትም ምክንያት ስለገንዘብ ሎጂካዊ ዕድገት ያለን አስተሳሰብ ዚተዛባ በመሆኑ ነው። ስለሆነም ዚአንድን አገር ዕድገት ኚዶላር ወይም ዛሬ ደግሞ ኚኊይሮ ጋር በማያያዝ ብቻ ነው ዕድገት ሊመጣ ይቜላል ዚሚቜል ዚተሳሳተ አባባል በመስፋፋቱ ብዙውን አሳስቷል። ባለፉት ስላሳና አርባ ዐመታት ዹውጭ ዕዳን በሚመለኚት በብድር አማካይነት ዕድገት እናመጣለን ያሉ አገሮቜ በመሉ ወደ ድህነትና ኢኮኖሚያ቞ውን ወደ ማዘበራሚቅ ነው ያመሩት። ዚመጚሚሻ መጚሚሻም እስኚዛሬም ድሚስ ዚወለድ ወለድ ኚፋዮቜ በመሆን ንጹህ ሀብታ቞ውን ለኢንዱስትሪ አገሮቜ ያስተላልፋሉ። ለምሳሌ እንደናይጀሪያና አንጎላ ዚመሳሰሉት በዘይት ሀብት፣ በወርቅና በዲያመንድ ዚተትሚፈሚፉ አገሮቜ ለምን ብድር እንደሚያስፈልጋ቞ው አይገባኝም። ለምንስ ለዕድገታ቞ው ኚሚያስፈልጋ቞ው በላይ ዘይት እያመሚቱ ዚአካባቢ ውድመትና መመሹዝ እንደሚያስኚትሉና ቜግር ውስጥ እንደሚገቡ በፍጹም ግልጜ አልሆነልኝም። ማለት ዚሚቻለው ግን ኚሙስና ባሻገር እነዚህ መንግስታት በውጭ ዚኮንሰልቲንግ ኩባንያዎቜና በዓለም አቀፍ ኢንስቲቱሜኖቜና ዓለም አቀፍ ኮሙኒቲው እዚተመኚሩ አገሮቻ቞ውን ወደሲኊልነት እዚለወጡ ነው።

ያም ሆነ ይህ ልክ እንደማንኛውም ምርት ገንዘብም ዹሰው ልጅ ጭንቅላትና ዚስራ ክፍፍል ውጀት ነው። ኚስራ-ክፍፍልና ኚንግድ በፊት ገንዘብ አልነበሚም። ዚተለያዩ ዚገንዘብ ዐይነቶቜም መፈጠር ዚቻሉት ዚስራ-ክፍፍል ውስብስብ እዚሆነ ስለመጣ ነው። ይህም ማለት ዚዛሬው በዓለም አቀፍ ደሹጃ በዚአገሮቜ ውስጥ ዚሚታተመው፣ ወይም ደግሞ ውጭ እዚታተመ ዚሚገባው ዚወሚቀት ገንዘብ- በቮክኖሎጂ ምክንያት ዚተነሳ፣ ብዙ ዚሶስተኛው ዓለም አገሮቜ ገንዘብ በቀላሉ ፎርጅ እንዳይደሚግ ዚሚያስላ቞ው ዚማተሚያ ቮክኖሎጂና ዹሰለጠነ ዹሰው ኃይል ዹላቾውም-  ዚታሪክ ውጀትና አስፈላጊነት ነው። ይህም ማለት ዚዛሬው ዚወሚቀት ገንዘብ በዚመንግስታቱ ወይም በማዕኹላዊ ባንኮቜ ካለምንም ድጋፍ በዕምነት ብቻ እዚታተመ እንደ አስፈላጊነቱ እንዲሜኚሚኚር ዹሚደሹግ ነው። ስለሆነም ዚገንዘብ መጠኑ በኢኮኖሚ ውስጥ በሚመሹተው ምርት አማካይነት እዚተመጠነ ይሜኚሚኚራል። በሌላ ወገን ደግሞ በተለያዩ መሳሪያዎቜ አማካይነት ወደ ኢኮኖሚው ውስጥ ዚተሜኚሚኚሚው ገንዘብ ወደባንኮቜ ይመለሳል። በባንክ፣ በተጠቃሚው፣ በነጋዮውና በአማርቹ መሀኹል በገንዘብ አማካይነት መተሳሰር ይፈጠራል። እንደ ኢኮኖሚው ዕድገት፣ በሳይንስና በቮክኖሎጂ ላይ ተመስርቶ መመሚትና አለመመሚት፣ እንዲሁም ዚውስጥ ገበያ መስፋፋትና አለመስፋፋት፣ መዳበርና አለመዳበር ዚገንዘብም ጥንካሬና አለመጠንኹር ይወሰናል። በአንድ አገር ውስጥ ዚገንዘቡ ዚመግዛት ኃይል ደካማ ነው ሲባል፣ ኢኮኖሚው በደካማ መሰሚት ላይ ሰለተገነባና ለገንዘቡ ዚጀርባ አጥንት መሆን ስለማይቜል እንጂ፣ ገንዘብ በራሱ ዚመግዛት ድክመት ዚለውም። ዹዋጋ ግሜበትም ዋናው ምንጭ ዚኢኮኖሚ ድክመት፣ ዚአመራሚት ዘዎ፣ በተመጣጠነ ዋጋ አለማምሚት (Cost Effectivness) ዚጥሬ-ሀብቶቜና ዚስራ ዋጋ መወደድና፣ ኹዚህ ጋር ተያይዞ በገበያ ላይ ዹሚቀርበው ምርት ዕጥሚትና ሌሎቜ በዓለም ገበያ ላይ ዚሚኚሰቱና በእኛ ኢኮኖሚ ላይ ዚሚኖራ቞ው ተፅዕኖ፣ ወዘተ… ለዋጋ ግሜበት ወይም መወደድ ምክንያት ይሆናሉ። በዚህ መልክ ብቻ ስለገንዘብ ዚመግዛት ኃይል ወይም ድክመት ማውራት ይቻላል። ገንዘብ ታትሞ ኢኮኖሚ ውስጥ ቢበተን ወይም ኹላይ ሆኖ በሄሊኮፕተር ቢበተን ዚግዎታ ይህ ጉዳይ ለግሜበት ምክንያት ሊሆን አይቜልም። በሌላ ወገን ዹተበተነውን ገንዘብ ኹፍተኛ ኃይል ባለው ቫኪዩም ክሊነር ኹላይ ሆነን ዹተወሰነውን ገንዘብ ብንመጠውና፣ ኚመሬት ላይ ደግሞ ያለውን ዚምርት መጠን ካልጚመርነውና (Ceteris Paribus) በድሮው መጠን ብቻ ዚሚቀርብ ኹሆነና ዹሰፊው ህዝብ ዚመግዛት ኃይል ካልጚመሚ ድሚስ ወይም በድሮው መልኩ ዚሚቀጥል ኹሆነ ይህ ማለት ዹዕህል ዋጋ ይቀንሳል ማለት አይደለም። ለዛሬው በአገራቜን ውስጥ ዹዋጋ ግሜበት ዋናው ተጠያቄ አገዛዙ ኚሃያ ሰባት ዐመት ጀምሮ ዚሚያካሂደው በዘሹፋ ላይ ዹተመሰሹተ ዚኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ በዚህም ዚተነሳ አጠቀላይ በሳይንስና በቮክኖሎጂ ላይ ዹተመሰሹተ ሰፋ ያለ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሎ አለመኖር፣ ዚአገልግሎቱ መስኩ መስፋፋት፣- ዚተጚባጭ ኢኮኖሚውን ዕድገት ዚሚያንፀባርቅ ወይም ዚሱ ተቀጥያ አይደለም- ዚትላልቅ ሆቮል ቀቶቜ መስፋፋትና እህል፣ ስጋና ቅቀ፣ ውሃና ሃይል እንዲሁም ልዩ ልዩ ለህዝቡ ዹሚጠቅሙ ነገሮቜን በኹፍተኛ ደሹጃ መጋራት፣ አዲስ መጀና ገንዘብ ያካበተ ኃይል ዚፍጆታ አጠቃቀም ኚአገሪቱ አጠቃላይ ዚኢኮኖሚ ዕድገት ጋር ሳይመጣጠን መጚመር፣ ዹውጭ ተራድዕ ድርጅቶቜና ዹዓለም አቀፍ ድርጅቶቜ ሰራተኞቜ ቁጥር መጹመርና ተጠቃሚ ኃይል መሆን፣ እነዚህ ሁሉ ሲደመሩ ዹዚህ ዐይነቱ ዚፍጆታ አጠቃቀም በምርት ዕድገት አለመካካስ ወዘተ… ለዋጋ ውድነት ተጠያቂዎቜ ናቾው ብሎ አፍን ሞልቶ መናገር ይቻላል።

እዚህ ላይ ለማለት ዹምፈልገው በገንዘብ ላይ ግልጜ አመለካኚትና ሎጂካዊ ዕድገቱን ኚተሚዳን ስለኢኮኖሚ ዕድገትም ዹሚኖሹውን ሚና መገንዘብ ይቻላል ማለት ነው። ኹዚህ ስንነሳ ባንኮቜን እንዎት ማደራጀት አለብን? እንዎትስ ለኢኮኖሚ ዕድገት ሊያግዙ ይቜላሉ? በምንስ መልክ አምራቹም ሆነ ነጋዮው በቂ ዚብድር ገንዘብ በዝቅተኛ ወለድ በመበደር ለኢኮኖሚው ዕድገት አስተዋፅዖ ማድሚግ ይቜላሉ? ዹሚለውን በቀላሉ መመለስ ይቻላል። በመጀመሪያ ደሚጃ፣ ማዕኹለኛ ባንክ አለ። ይህ ገንዘብ ዚሚያትምና ለባንኮቜ በትንሜ ወለድ ዚሚያኚፋፍል ነው። በሁለተኛ ደሚጃ፣ በግል ዚሚንቀሳቀሱ ዚንግድ ባንኮቜ ዚሚባሉ አሉ። በሶስተኛ ደሚጃ፣ በመንግስት ቁጥጥር ስር፣ በክፍላተ-ሀገራትና በሎካል ደሹጃ ለማዕኹለኛና ለትናንሜ ኢንዱስትሪዎቜ ብድር ዚሚያበድሩ ይኖራሉ። ኹማዕኹላዊ ባንክ ዚገንዘብ ክፍፍል ባሻገር እነዚህ ሁለቱም ዚባንክ ዘርፎቜ በመያዣ (Bond) መልክ ወለድ በመክፈል ገንዘብ ካለው በመበደር እንደገና ብድር ለሚፈልገው ገንዘብ ያበድራሉ። ኹዚህ በተጚማሪ በደሞዝ ተቀጥሮ ዚሚሰራው ሰራተኛ ገንዘቡን በባንክ አማካይነት ያገኛል። ዹተወሰነውን ደግሞ በቁጠባ መልክ ያስቀምጣል። አስ቞ጋሪው ነገር በአገራቜን ውስጥ አብዛኛው ሰራተኛ በባንክ አማካይነት ደሞዙ አይኚፈለውም። አብዛኛውም ዚመቆጠብ ኃይሉም ደካማ ነው። ስለዚህም ዹማዕኹላዊ ባንኩና ዹተወሰነው ሀብታም ዚህብሚተሰብ ክፍል ለኢኮኖሚው ዕድገት አስተዋፅዖ ኹፍተኛ ሚና ይጫወታሉ ማለት ነው። ኹዚህ በተሹፈ ዹውጭ ምንዛሪን መቆጣጠርና ለኢኮኖሚው ዕድገት ብቻ እንዲውል ማድሚግ። ለማሜንና ለቮክኖሎጂ እንዲሁም ለጥሬ-ሀብት ማስመጫ ካልሆነ በስተቀር ለቅንጊት እዚተባለ ዹውጭ ምንዛሪ እንዳይባክን መቆጣጠር ያስፈልጋል። ኹዚህም በላይ ዚጥሬ ሀብቶቜን በመላክ  ዹውጭ ምንዛሪ ማግኘት ይቻላል። ያም ሆነ ይህ ለአንድ አገር ዚኢኮኖሚ ዕድገት ዹአገር ውስጥ ገንዘብ ነው ውሳኙ። ዶላርና ኊይሮ አይደሉም። ኹዚህ በመነሳት በዓለም አቀፍ ደሹጃ ስለ ዕድገት ዹሚነፍሰውን ዚተሳሳተ አባባል በመጠኑም ቢሆን እንመልኚት።

 

ምን ዐይነት ዕድገት፣ ዕድገት ለማን!

እስኚዛሬ ድሚስ በአገራቜን ምድር አንዳቜ ዐይነት ዕድገትን ለማምጣት ተብለው ተግባራዊ ዹሆኑ ፖሊሲዎቜና ፕሮግራሞቜ በሙሉ በውጭ ኃይሎቜ ዚታቀዱና ዚጥቂቱን ዚህብሚተሰብ ክፍል ጥቅም ብቻ ዚሚያንፀባርቁ ና቞ው። በተለይም ግሎባል ካፒታሊዝም በአሞናፊነት ኚወጣ ካለፉት 60 ዓመታት ጀምሮ በብዙ ዚሶስተኛው ዓለም አገሮቜ ተግባራዊ ዚሆኑት ፖሊሲዎቜ በሙሉ በአወቅሁኝ ባይነት ዚተካሄዱና አሉታዊ ባህርይ ያላ቞ው ና቞ው። ዚዚአገሮቜን ታሪክ፣ ባህል፣ ዚዕውቀት ደሹጃና ዚምጣኔ ሀብት ግኝት በማጥናት ዹተኹናወኑ አይደሉም። በመሰሚቱ ኹሁለተኛው ዓለም ጊርነት በኋላ ዹተዋቀሹውን ዹዓለም ኢኮኖሚ እንዲያግዙ ሆነው ዹተዘጋጁ ሞዎሎቜ በመሆናቾው ሀብትን መጣቜና አውዳሚ ሊሆኑ በቅተዋል። በዚህም ምክንያት በዚአስር ዐመቱ ስማ቞ውን እዚለዋወጡ ዚሚወጡት ፖሮግራሞቜ ዚባሰውን ድህነትን ፈልፋይ በመሆን ለሀብት መባኚንና ለብዙ ሚሊዮን ህዝቊቜ መሞትና መሰደድ ምክንያት ሆነዋል። ዚባሰውኑም ጥገኛ በማድሚግ ለብሄራዊ ነጻነት መቩርቩርና ለግለሰብአዊ ነጻነት እጊት ዋነኛ ምክንያት ሆነዋል። ዛሬ በዚአገሮቜ ውስጥ አገራቜንም ጚምሮ አምባገነን መንግስታት ዚሰፈኑትና በአስፈሪ መሳሪያ በመታጠቅና በተወሳሰበ ዚስለላ ድርጅትና መሳሪያ ዚሚያሰቃዩት በዚአገሮቹ ውስጥ ዹፈለቁ ሳይሆኑ ኹውጭ በመጣ መሳሪያና በውጭ ኃይል በመታገዝ ነው። ይህም ማለት ኹውጭ በዕድገት ስም ዚሚመጣው ፖሊሲ ኚኢኮኖሚ አልፎ ብሄራዊ ነፃነትንና ዚግለሰብ ነፃነትን በመግፈፍ ለዘለዓለማዊ ድህነት ዚሚዳርግ ነው። በመሆኑም እስኚዛሬ ድሚስ፣ በተለይም ባለፉት ሃያ ሰባት ዐመታት በአገራቜን ምድር ተግባራዊ ዹሆነው ዚኢኮኖሚ ፖሊሲ ኹመጹቆኛ መሳሪያዎቜና ስልቶቜ ጋር በመጣመርና ሰፊውን ህዝብ፣ በተለይም ዹኹተማውን ህዝብ በነፃ ገበያ ስም በማታላል ዹጭቆና ኢኮኖሚን ያስፋፋና ቎ክኖሎጂያዊ ዕድገት እንዳይኖር እንቅፋት ዹሆነ ነው።

ኹዚህ ቀደም አንዳንድ ቊታ ላይ ለማሳዚት እንደሞኚርኩት አገራቜን እስኚዛሬ ዚተኚተለቜውና ወደፊትም መኹተል ዚሚገባትን ዚኢኮኖሚና ዚህብሚተሰብ ፖሊሲ በሚመለኚት በምሁሩ ዘንድ ውይይት፣ ጥናትና ክርክር ሲካሄድ በፍጹም አይታይም። አብዛኛው ማለት ይቻላል፣ ዚእነ ዓለም አቀፍ ዚገንዘብ ድርጅት ስታትስቲኮቜን ኚማገላበጥ አልፎ ለአገሩ ጠበቃ በመሆን በአገር ወዳድነት ስሜት ትንተና ሲሰጥና ሲያስተምር በፍጹም አይታይም። አብዛኛዎቻቜን ውጭም ብንማርና ውጭ አገር አዚሰራን ብንኖር፣ እስኚተወሰነም ደሹጃ ድሚስ ዚኢትዮጵያ ህዝብ እንድንማር ቀሚጥ ኚፍሎልናል። ትምህርት ቀት አስርቶልናል። ተምሹንና አውቀን መልሰን እንድንሚዳው፣ ኚድንቁርናና ኚድህነት እንድናላቅቀው ነው ይህንን ሁሉ ያደሚገልን። ብሄራዊ ነፃነቷ ዚተኚበሚቜና ዚሰለጠነቜ ኢትዮጵያን እንድንገነባለት ነው ይጠባበቅ ዚነበሚው። ይህንን ኚማድሚግ ይልቅ ብቻውን እንዲጋፈጥ አድርገነዋል። ማንም እዚመጣ እንዲጚፍርበት አድርገናል። ሳናውቀው ኹውጭ ኃይሎቜ ጋር በመተባበር ዚኢትዮጵያ ህዝብ በድህነት ዓለም ውስጥ እንዲኖር ለማድሚግ በቅተናልፀ አዋርደነዋልም።

በመሰሚቱ ኚአውሮፓ ምሁራን ብዙ ነገሮቜ በተማርን ነበር። በአውሮፓ ታሪክ ውስጥ መንግስታት ኹፍተኛ ሚና ቢጫወቱም፣ ቀዳሚውን ሚና ዚተጫወቱት ግለሰቊቜ ና቞ው። ማንም ሳይገፋፋ቞ው በራሳ቞ው ጥሚትና ውስጣዊ ግፊት ዚጥበብን ምስጢር በመፈለግ ዚግዎታ ህዝባቜንን ኹጹለማ ማውጣት አለብን በማለት ዚብርሃኑን መንገድ ያሳዩት ግለሰብ ምሁራን ና቞ው። ኚኩዛኑስ እስኚ ዳን቎፣ ኚዳቪንቺ እስኚ ሚካኀል ኀንጀሎ፣ ኚኬፕለር እስኚ ኒውተንና ላይብኒዝ፣ ዹኋላ ኋላም ሺለር፣ ጎተና ካንት፣ አንደዚሁም ብዙ ዚጥበብና ዚድራማ ሰዎቜ ብቅ ያሉትና ህብሚተሰቊቻ቞ውን ለመለወጥ ዚተነሳሱት መንግስታት ስለቀሰቅሷ቞ውና ስላገዟ቞ው አልነበሚም። ዚዚግለስቊቹ ጥሚት ነው። ጹለማንና ፊዩዳላዊ ዚድንቁርናን፣ አንዲሁም ዚካቶሊክን ጭፍን ሃይማኖት በመቃወም ነው በሳይንስ ላይ መሚባሚን ዚጀመሩት። ዚዚግለሰቊቜን ታሪክ ስንመሚመር፣ አንዳንዶቹ ዚጻፉትን ሁሉ ለማሳተምና ለመበተን እዚተ቞ገሩ፣ እንዲሁም እንዳይነቃባ቞ው እዚተሰደዱ በመኖር ዚቜግርን ፅዋ ይቀምሱ ነበር። በማያቋርጥ ትግል ግን በመጚሚሻ ላይ ለአውሮፓ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ለእኛም ዹሚተርፍ ሳይንስና ጥበብ ጥለውልን አልፈዋል። ዕውቀታ቞ው ዓለም አቀፋዊ ባህርይ እንዲኖሚው አድርገዋል። ዘለዓለማዊ ነው። በህልማቾው ውስጥ ለአውሮፓ ብቻ ብለው አስበው ዚፈጠሩት ዕውቀት ሳይሆን፣ ኚፍልስፍና እስኚድራማ ድሚስ ያለውን ግኝት ስንመለኚት ዹሰውን ልጅ ባህርይ ዚሚመለኚትና፣ ኚተፈጥሮ ጋር ያለውን ግኑኝነት ግንዛቀ ውስጥ ያገባ ነው። በመስሚቱ ዚአውሮፓ ዚጥንቱ ዕውቀት፣ ታላቁ ዹሮኔጋል ሳይንቲስትና ፈላስፋ አንታይ ዲዮፕ እንደሚያስተምሚን፣ ኚግብጜ ዹተወሰደ ነው። ግሪኮቜ ይህንን በመውሰድ ነው ያስፋፉት። ኚዚያም አውሮፓውያኖቜ ዹበለጠ ውስጠ-ኃይል በመስጠት ለካፒታሊዝም ዕድገት ይጠቀሙበታል። በሌላ አነጋገር ትግሉ ዕውቀታቜንን መልሶ ዚማግኘት ትግል ነው።  ስለሆነም ወደ ኋላ ተመልሰን ታሪካቜንን ማጥናት ይኖርብናል። ምናልባትም ለዛሬው ቜግራቜን መልስ ሊሰጠን ይቜላል ብዩ እገምታለሁ።

እዚህ ላይ ጥንቃቄ ማድሚግ ያለብን ይመስለኛል። ካፒታሊዝም ሙሉ በሙሉ ሳይንቲስቶቜ ያዳበሩትን በስምምነትና በስርዓት ላይ ዚተመሰሚተ፣ እንዲሁም ኚተፈጥሮ ጋር ዹሚኖሹውን ስምምነት በመጣስ ተፈጥሮንና ዹሰውን ልጅ ወደ ተበዝባዥነት ለውጧ቞ዋል። ዹሰውም ልጅ ህይወት ሙሉ በሙሉ ማ቎ሪያላዊ እንዲሆን በማድሚግ ዹሰው በሰው ግኑኝነት ወድ ንጹህ ዚገንዘብ ግኑኝነት እንዲለወጥ አድርጓል። በዚህም ዚተነሳ በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደሹጃ ኹፍተኛ ዹህሊና ቀውስና ዚአካባቢ መበላሞት እንዲደርስ አድርጓል። በዚህ ብቻ ሳይወሰን ኚሚዥም ጊዜ ጀምሮ በዓለም አቀፍ ደሹጃ ዚሚካሄደው ጊርነት ዚጥሬ-ሀብትን ኚመቆጣጠር ጋር ዚተያያዘ ነው ማለት ይቻላል። በብዙ ዚሶስተኛው ዓለም አገሮቜ ዚሚካሄዱት ዚእርስ በርስ ጊርነቶቜ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ዹውክልና ጊርነቶቜ ና቞ው። ስለዚህም ለህብሚተሰብአቜን ዕድገት በመንታገልበት ጊዜ ብዙ ነገሮቜን ማውጣትና ማውሚድ ይኖርብናል ማለት ነው። ምን ዐይነት ዚህብሚተሰብ ሞዮል ነው ለአገራቜን ዚሚያዋጣው እያልን ማጥናትና መኚራኚር ይኖርብናል። በአደገውም ዚካፒታሊስት ህብሚተስብም ውስጥ አዲስ ሞዮልን ለመፈለግ ትግል እዚተካሄደ ነው።

ኹዚህ ስንነሳ ካፒታሊዝም ዹሰው ልጅ ዕድገትና ስልጣኔ ዚመጚሚሻው ቊታ ላይ አልደሚሰም። ስለሆነም ካፒታሊዝም ዚመጚሚሻው፣ ዚታሪክም መፈጞሚያው ላይ ነን ብለን ልናቆምና ነገሹ ዓለሙን በሙሉ ልንተው አንቜልም። ታሪክ ሂደት ነው። ክንዋኔ ነው። ዹሰው ልጅ አንድን ነገር እስኪያገኝ ድሚስ ሳያቋርጥ ይፈልጋል። ህይወታቜንና ዹሰው ልጅ ታሪክ እንደ ወንዝ ውሃ ፈሳሜ ና቞ው። ኹዚህ ስንነሳ ዚህብሚተሳብቜን ዚወደፊት ዕጣ ምን ይመስላል? ለመጭው ትውልድስ ምን ጥለንለት ነው ማለፍ ያለብንና? ዚምንቜለው? ብለን ማውጣትና ማውሚድ ይኖርብናል።

በእርግጥ አሁን በአለው እጅግ ዚተወሳሰበና ግራ ዚሚያጋባ ዓለም ዚዚአገሮቜን ዚወደፊት ዕድል መወሰን ያስ቞ግራል። ሁሉም ነገር ኚገበያ አንፃር በሚታሰብበት ዓለም ስልጣኔና ዹሰው ልጅ ትርጉም እያጡ መጥተዋል። ዚዚአገሮቜ ዕድገት መለኪያ ንግድና ብዙ ትርፍ ማካበት ሆነዋል። ውብ ውብ ኚተማዎቜ፣ ጥበብና ድራማ፣ ለሰው ልጅ ዚሚስማሙና፣ ኚአካባቢውና ኚአዚሩ ሁኔታ ጋር ዚሚሄዱ ዚቀት አሰራሮቜ ኚሚዥም ጊዜ አንፃር ታስበው አይሰሩም። በእኛ አገርና በሌሎቜ ዚሶስተኛው ዓለም አገሮቜ ያለው ኹፍተኛ ምሁራዊ ክፍተት ኢንቬስተር ነን ዚሚሉት እንደፈለጋ቞ው እዚገቡ እንዲፈተፍቱ አመቺ ሁኔታ ፈጥሮላ቞ዋል። በዚህም ምክንያት ዚተነሳ ሰፊው ህዝብ በአገሩና ለሀብቱ ባይተዋር በመሆን፣ እንዲሁም ደግሞ በፍርሃት በመዋጥ በአሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ እንዲኖር ተገዷል። አገሮቜና ህዝብ ታሪክ ዚሚሰራባ቞ውን ዚሚሰሩ መሆናቾው ቀርቶ ጥቂት አዋቂ ነን ባዮቜ ውስጥ ካለው ኃይል ጋር ዚእጅና ጓንቲ በመሆን አገር እያፈራሚሱ ነው። ይህንን ዐይን ያወጣና ታሪኚ-ቢስ ተግባር ዹሚቃወሙ ደግሞ አናርኪስቶቜና አሞባሪዎቜ ወይም ግራዎቜ አዚተባሉ ይወነጀላሉ። ይህን ሁሉ ዹሚመለኹተው ነገሩን ባለመሚዳት ዝም ብሎ “ሌሎቜ ሲዘርፉ እኔም አብሬ ልዝሹፍ“ በማለት አብሮ አገር ያወድማልፀ ታሪክ ያበላሻል። ይህንን ዐይነቱን እጅግ ዹዘገነነ ሁኔታ እስኚመቌ ድሚስ ነው ውጩ ዹሚተኛው?  በካፒታሊስት አገሮቜም ኢንቬስተሮቜ ነን ዹሚሉ ብዙ ነገሮቜን እዚተቆጣጠሩና እያበላሹ መጥተዋል። ይህንን አስመልክቶ ሰሞኑን እዚህ ዚምኖርበት ኹተማ ውስጥ ዹቀኝ ኮንሰርቫቲቊቜ፣ ዘ ወርልድ ዚሚባለው ጋዜጣ ላይ ታትሞ ዚወጣ፣ ስለቀት አዲስ  ዚአሰራር ባህል ላይ ሰፊ ዘገባ ቀርቧል። በትንተናው መሰሚት ባለፉት ሰላሳ ዐመታት ኚንጹህ ዚኢኮኖሚና ዚትርፍ አንጻር ብቻ ታስበው ዚሚሰሩ ቀቶቜ ዚዚኚተማዎቜን ስዕሎቜ እንደቀዚሯ቞ውና፣ በሰው ዹህሊና አወቃቀር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደር እንደቻሉ ይዘግባል። ኹማዕኹለኛው ዘመን ጀምሮ ሲወርድ ሲዋሚድ ኚመጣው ዚመኖሪያ ቀቶቜ አሰራር፣ ሱቆቜና ትላልቅ ዚመንግስታት ህንጻዎቜ ጋር ያወዳድራል። በመሆኑም ይላል፣ ዚሚሰሩት አዳዲስ ህንጻዎቜ በሙሉ ዹተወሰነ ዚጂኊሜትሪን ቅርጜ ዹማይኹተሉና ሀርሞኒዚስ ባህርይ ዚሌላቜውና እንዲሁም ዘላቂነት እንደሌላ቞ ቁልጭ አድርጎ ያስቀምጣል። በሌላ ወገን ደግሞ በጥንቱ ዘመን መኖር፣ ዕውቀት መቅሰም፣ ባህላዊ ክንዋኔዎቜ፣ መጻህፍት ቀቶቜ፣ ዚሚያማምሩ ቡና ቀቶቜ ወዘተ… አንድ ላይ ሆነው ዚሚገነቡ ነበሩ በማለት ትዝታ ውስጥ ይኚተናል። ትላልቅ ግቢዎቜ፣ ሰፊ ጓሮ ሲኖራ቞ው  ኗሪውን ዚሚያገናኙ ነበሩ። ዚዛሬው ዹህንፃ አሰራር ኚኢኮኖሚ አንጻር ብቻ ዚሚሰራ በመሆኑ ዚኚተማዎቜን ውበት እያበላሞና ዚህዝቡን ዚማሰብ ኃይል እያዘበራሚቀው ነው በማለት ያለውን ቅሬታ ያስቀምጣል። ይህም ዚሚያመለክተው ዕድገትንና አጠቃላይ ዹሆነን ዚኑሮ ስልት በሚመለኚት አሁንም ውይይት ይካሄዳል። ጥቂት አዋቂ ነን ዹሚሉ ሰዎቜ በአንድ አገር ላይ መወሰን እንደሌለባ቞ው ያመልክታል። ይህ ዐይነቱ ክርክር ኚኢኖሚክስ አንስቶ እስኚትምህርትና፣ እስኚሌሎቜም ድሚስ ዹሚዘልቅ ነው። ጥቂት ኀሊት ነኝ በሚለው፣ በኀንቚስተሮቜና በህዝቡና ሰፊ ምሁራዊ ዕውቀት ባላ቞ው ዘንድ ዹጩፈ ክርክር ይካሄዳል።

ያም ሆነ ይህ  ለዕድገት ዹሚደሹገው ትግል እስ቞ጋሪ ነው። ምሁራዊ ዹሆነ ግልጜ ውይይት በማይካሄድበት በእንደኛ ባለ አገር ውስጥ ዚዕድገትን ሂደትና ዓለምን በሁለት አማራጮቜ ብቻ ወስኖ ማውራት ዹተለመደ ሆኗል። ይኾውም በገበያ ኢኮኖሚና በሶሻሊዝም መሀኹል ዹሚደሹግ ትግል ነው ዹሚል ነው። በሌላ ወገን ደግሞ ስለገበያ ኢኮኖሚ ያለው አመለካኚት ግልጜ በሆነ መልክ ተተንቶኖ አይቀርብም። በአብዛኛዎቻቜን ዘንድ ዚገበያ ኢኮኖሚ ዹሚለው ግዙፍ አባባል ኚንግድ ጋር ብቻ ተያይዞ ነው ዚሚታዚው። ይህም ማለት በንግድ ላይ በሚመሚኮዝ፣ ዛሬ በብዙ ዚአፍሪካ አገሮቜ እንደሚታዚው ዚገበያ ኢኮኖሚ እዚተባለ በሚወራውና በንጹህ ዚካፒታሊስት ኢኮኖሚ ላይ ያለው ግንዛቀ ግልጜ  አይደለም። አብዛኛው ዚትኛውን እንደሚፈልግ አይነግሚንምፀ መንገዱንም አያሳዚንም።

ይህንን ውዝንብር ትተን ኹላይ ቀደም ብዬ ለማሳዚት እንደመኮርኩት ዚኢትዮጵያን ዚኢኮኖሚ ዚወደፊት ዕርምጃና ዚሚያዋጣውን ነገር ለመጠቆም ኚንጹህ ዚኢኮኖሚ ስሌት ብቻ መነሳቱ በጣም አደገኛ አካሄድ ነው። መነሳት ያለብንና መንደፍም ያለብን ዕቅድ ጠቅላላውን ኢትዮጵያ እንደ ብሄራዊ፣ እንደሀብሚተሰብአዊ፣ እንደማሀበራዊ፣ እንደባህልና እንደስነምግባራዊ ፕሮጀክት በመውሰድ ብቻ ነው። በዚህ ዐይነቱ ስፊ ፕሮጀክት ውስጥ ለግለሰብአዊ መብት፣ ለነጻ ኢኮኖሚ እንቅስቃሎ፣ በህብሚት ለሚካሄድና በመንግስት በሚደገፍ እያለን እዚነጣጠልን ማስቀመጥ እንቜላለን። ዚገበያ ኢኮኖሚ ዹሚለውም ፅንሰ-ሃስብ በዚህ ዹሚጠቃለል ሲሆን፣ ዋና አንቀሳቃሜ ሃይል ማኑፋክቱር ነው። ዚትናንሜና ዹማዕኹልኛ ኢንዱስትሪዎቜ፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ ዹዕደ-ጥበብ ሙያዎቜ ዚሚስፋፉበት ይሆናል። ይህ ዐይነቱ ኢኮኖሚዊ ክንዋኔና አንቅስቃሎ ወደ ካፒታሊዝም ያምራ አያምራ ኚዛሬውኑ ልንወስን አንቜልም። ዚዛሬውን ህልማቜንና ጅማሮአቜንን አዳዲስ ኃይሎቜ በመምጣት ሊያፈራሱት ይቜላሉ። ኚሞትን በኋላ መቃብር ውስጥ ሆነን ምን እንደሚሰሩ ልናያ቞ውና ልንቆጣጠራ቞ው አንቜልም። በሌላ ወገን ግን ኚብዙ አገሮቜ ልምድ መማር እንደሚቻለው፣ አንድ እንደባህል ዹተወሰደ አሰራርና ሰፋ ያለው ምሁራዊ እንቅስቃሎ ያለው ህብሚተሰብ ማንም እዚመጣ ዚሚጚፍርበት አገር አይሆንም። ብዙ ዚሚያበላሹ ነገሮቜና ኃይሎቜን በምሁራዊ ኃይልና ክርክር መግታት ይቻላል። ኹዚህ ስንነሳ ሰፋ ያለ ዚሲቪል ህብሚተሰብ መቋቋም አለበት። በዚህ አማካይነት ብቻና፣ ህበሚተሰብአዊ ባህርይ ያለው ኢንስቲቱሜንና አገዛዝ ኹተመሰሹተ ዚህብሚተሰብአቜን ዚዕድገት ጉዞ ዹተቃና ይሆናል።  መልካም ንባብ!

fekadubekele@gmx.de

 

ማሳሰቢያፀ በዚህ መልክ ወደ ፊት ጥናታዊ ጜሁፍ እንዲቀርብ ለሚፈልጉና አገርቀትም ይህ ዐይነቱ ጥናትና ምርምር በተቋም ደሹጃ እንዲስፋፋ ኹተፈለገ ዚግዎታ ሰፋ ያለ ዚማ቎ሪያል ድጋፍ ያስፈልጋል። እንደዚህ ዐይነቱ ጥናትና ምርምር በአንድ ሰው ትኚሻ ላይ ብቻ ሊወድቅ አይቜልም። በጣም አድካሚና ዚራስን ሀብት ዚሚጚርስ ነው። ዚግዎታ ተባብሮና ተደጋግፎ መስራት ያስፈልጋል።

 

AFRICA  DEVELOPMENT                                      

CONSULTING

 

 ADC  Dr. Fekadu Bekele

E-Mail: fekadubekele@gmx.de

Bank: Berliner Sparkasse. IBAN: DE13 1005 0000 032 032 5539

HOLISTIC MODEL-AFRICAN RENAISSANCE

  • Resource Based Development &Human Power
  • Organic Growth/ from bottom upwards
  • Science & Technology/Innovation
  • Entrepreneurship
  • Finance & Money
  • Institution/The Role of Government
  • Environment & Social